Friday, April 30, 2010

ቅዱስ ጊዮርጊስ

የቅዱስ ጊዮርጊስ አባቱ መስፍን ሲሆን ሲሙም አንስጣስዮስ ይባላል አገሩም ቀጰዶቅያ ሲሆን እናቱም ቴዎብስታ ትባላለች እሱአም ከፍልስጤም አገር ናት ከዛም ትንሽ ሆኖ ሳለ አባቱ አረፈ: 20 አመትም በሆነው ግዜ የአባቱን ሹመት ሊቀበል ወደ ንጉስ ዱድያኖስ ዘንድ ሄደ:ንጉሱም ጣዖት አቁሞ ጣዖትን እንዲያመልኩ ሰዎችን ሲያስገድዳችው አገኘው:ይህንን አይቶ ቅዱስ ጊዮርጊስ አዘነ በርሱ ዘንድ ያለውን ገንዘቡን ሁሉ ለድሆች ለምስኪኖች ሰጠ ባሮቹንም ነጻ አወጣቸው:ከዛም በንጉስ ፊት ቆሞ በክብር ባለቤት በጌታችን በመድሃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ:ንጉሱም አባበለው ብዙ ቃል ኪዳንም ገባለት እርሱ ግን አልተቀበለውም:ለመስማት እንኩአን የሚያስጨንቅ ስቃይን አሰቃየው ጌታችን ግን ሁሌም ያጸናዋል ቁስሉንም ያድነዋል:3 ግዜ እንደሚሞት እሱም እንደሚያስነሳው በአራተኛውም የምስክርነት አክሊልን እንደሚቀበል ነገረው:ቃል ኪዳንም ሰጠው ስሙ በአለም ሁሉ የተገለጠ ይሆን ዘንድ:በተጋድሎ እና መከራ በመቀበል ሰባት አመት እንደሚኖር መላእክትም እንደሚአገለግሉት ነገረው: ንጉሱም ባለመታዘዙ እና ባለመመለሱ እጅግ አዘነ ስለዚህም አትናስዮስ የሚባል ስራየኛ አመጣና እርሱም መርዝን ቀምሞ በጽዋ ሞልቶ አስማቱን ደግሞ እንዲጠጣ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰጠው:ወዲያውኑ የሚሞት መስሎት ነበር ቅዱሱም ያንን ጽዋ በጌታችን ስም አማትቦ ጠጣው ምንም ጉዳት አልደረሰበትም:ያ መሰርይም በክብር ባለቤት በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ ወዲያው ሰማእት ሆኖ አረፈ:ያንንም ተአምር አይተው ብዙዎች ሰዎች በሰማእትነት ሞተው የህይወት አክሊል ተቀበሉ ቁጥራቸውም 30,700 ነፍሳት ናቸው:ቅዱስ ጊዮርጊስም በዱድያኖስና በሰባው ነገስታት ፊት በቆመ ግዜ በዚያም የተቀመጡባቸው ወንበሮች ነበሩ ቅዱሱንም እሊህን የተቀመጥንባቸው ወንበሮች እንዲበቅሉና እንዲያብቡ እንዲያፈሩም ታደርጋቸው ዘንድ ካንተ እንሻለን አሉት:በዚአን ግዜም ጸልዮ እንዳሉት አለመለመው ይህንን ድንቅ ስራ አይተው ቁጥር የሌላቸው ብዙ አህዛብ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ:ከዛም ቅዱሱን ወስደው በጎድጉአዳ ምጣድ ውስጥ አበሰሉት:አቃጥለው አሳርረውም ስጋውንንና አጥንቱን ፈጭተው አመድ አድርገው ከረጅም ተራራ ላይ በተኑት:ጌታችንም ነፍሱን ወደ ስጋው መልሱአት ደግሞ አስነሳው:ወደ ነገስታቱም ተመልሶ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አስተማረ ቁትር የሌላቸው አህዛብ አደነቁ በጌታችንም አምነው በሰማእትነት ሞቱ:ነገስታቱም ደግመው ሙታኖችን ብታስነሳ አምላክህ እውነተኛ አምላክ እንደሆነ እናምናለን በርሱም እናምናለን አሉት ቅዱሱም ጸለየ ከጉድጉአድም ውስጥ ወንዶችና ሴቶችን ጎልማሶችንም አስነሳላቸው እነዛም በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አስተማሩ የገሃነምንም ወሬ ተናገሩ ጥምቀትንም ተቀብለው ተመልሰው አረፉ: ከሃድያን ነገስታቱ ግን ሙታንን ያስነሳህ አይደለም የረቀቁ ሰይጣናትን አሳየህ እንጂ ብለው ተከራከሩ ከዚአም ከጭንቀታቸው ብዛት የተነሳ ከአንዲት ደሃ ሴት ዘንድ አስጠበቁት እሱአም እንጀራ ልትለምንለት ወጣች የእግዚአብሄርም መልኣክ በላዩ ከበጎ ነገር ሁሉ የተመላ መኣድ አቀረበለት የዚያች መበለትም የቤቱአ ምሰሶ ቅርንጫፍን አበቀለ ታላቅ ዛፍም ሆነ ያችም መበለት በተመለሰች ግዜ የቤቱአ ምሰሶ ቅርንጫፍ አብቅሎ ታላቅ ዛፍ እንደሆነ ሲለማእዱም ይህን ታላቅ ምልክት አይታ የክርስቲያኖች አምላክ ሰው ተመስሎ ወደ እኔ መጣ አለች ቅዱሱም እኔ አምላክ አይደለውም የአምላክ ባርያ ነኝ እንጂ አላት እሱአም እንዲ ብላ ለመነችው የአምላክ አገልጋይ ከሆንክ ችርነትህ እንድትደርሰኝ እለምንሃለው እውር ደንቆሮ ድዳ ጎባጣ የሆነ ልጅ አለኝ እና ታድንልኝ ዘንድ እለምንሃለው ስለጌታችን እምነትም አስተማራትና መበስቀል ምልክት አማተበው ያን ግዜም ልጁ አየ ቅዱሱም በሌላ ግዜ እንዲሰማ እንዲናገር እና እንዲሄድ እንዲያገለግለኝም እኔ እሻለው አልት በዚአን ግዜ ንጉሱ በአገሩ መዳ ውስጥ ሲዘዋወር ያችን ዛፍ አይቶ አደነቀ ስለሱአም ጠየቀ ቅዱስ ጊዮርጊስ በሱአ ዘንድ የተቀመጠባት የዚያች መበለት የቤቱአ ምሰሶ እንደሆነ ነገሩት ንጉሱም ተቆጣ ቅዱሱንም ከዚያ ወስዶ አስገረፈው በመንኮራኩርም አበራዩት ሞቶም ከከተማ ውጩ ጣሉት ጌታም ከሞት አስነሳው ወደ ነገስታቱም ተመለሰ ንጉሱም አይቶ ደነገጠ ስለህይወቱም አደነቀ ከዚያም በሁአላ ይሸነግለው ዘንድ ጀመረ በመንግስቱ ላይም ሁለተኛ ያደርገው ዘንድ ቃል ገባለት ቅዱስ ጊዮርጊሲም እየዘበተበት ነገ በጠዋት ለአምልክቶችህ መስዋትን አቀርባለው አንተም ህዝብ እንዲሰበሰቡ እዘዝ እኔ ስሰዋ እንዲያዩ አለው:ንጉሱም እውነት የሚሰዋ መስሎት ደስ አለው ወደ ቤተ መንግስቱም እልፊኝ አስገብቶ አሳደረው ለጸሎትም ተነሳ የዳዊትንም መዝሙር አነበበ የዱድያኖስ ሚስቱ እለእስክንድርያ ንግስት ሰምታ ቃሉ ደስ አሰኛት የሚያነበውንም ይተረጉምላት ዘንድ ለመነችው እርሱም እግዚአብሄር አለምን ከፈጠረበት ሰው እስከሆነበት ግዜ የሆነውን ሁሉ ያስረዳት ጀመር ትምህርቱም በልቡአ ተቀርጾ በክብር ባለቤት በጌታችን አመነች በማግስቱም ቅዱስ ጊዮርጊስ ለአማልክት ሲሰዋ ለማየት ሰው ሁሉ እንዲሰበሰብ አዋጅ ነጋሪ ዞረ የበቱአን ሚሰሶ ያበቀለላት ያቺ መበለት ሰምታ እውነት መስሉአት እጅግ እያዘነች ልጁአን ተሸክማ እያለቀሰችም ወጣች ቅዱስ ጊዮርጊስም ባያት ግዜ ፈገግ አለ ልጅሽን በምድር ላይ አኑሪው አላት ከዛም ልጁአን ጠርቶ ወደ አጵሎን ሂድ ወደ እኔም ይመጣ ዘንድ በክብር ባለቤት በጌታዬ ኢየሱስ ስም እዘዘው አለው ያን ግዜ ያ ልጅ ድኖ ቅዱስ ጊዮርጊስ እንደ አዘዘው ወደ ጣዎቱ ቦታ ሄዶ አዛዘው በጣዖቱ ያደረ እርኩስ መንፈስም ከማደሪአው ወቶ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወዳለበት መቶ እኔ ሰውን ሁሉ የማስት እንጂ አምላክ አይደለውም ብሎ በህዝብ ሁሉ ፊት አመነ ቅዱሱም ትውጠው ዘንድ ምድርን አዘዛትና ወዲያውኑ ዋጠችው ጣዖታቱንም ከአገልጋዮቻቸው ጋር አጠፋቸው ንጉሱም ከወገኖቹ ጋር አፈረ:ብስጭት እና ቁታንም እንደተመላ ወደ ንግስት ምስቱ ዘንድ ገባ እሱአም አምላካቸው ጽኑ እና ሃያል ነውና ክርስቲያኖችን አትጥላቸው አላልኩህምን አለችው ይህንንም ከሱአ ሰምቶ በርሱአ ላይ እጂግ ተቆጣ ወደ ክብር ባለበት ክርስቶስ እምነት የከበረ ጊዮርጊስ እንደአስገባት አወቀ ከዚም በሁአላ ከከተማ ውጪ እንዲጎትቱአት እና በመጋዝም እንዲሰነጥኩአት አዘዘ የሰማእትነትንም አክሊልንም በመንግስተ ሰማያት ተቀበለች በዚያን ግዜ ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ስራ ነገስታቱ ሁሉም ደነገጡ ሃፍረት ደግሞ እንዳይጨምርባቸው ከርሱም እንድያርፍ ራሱን በስይፍ ይቆረጥ ዘንድ እንዲጽፍ ንጉስ ዱድያኖስን መከሩት ያን ግዜም የክብር ጊዮርጊስን ራስ በሰይፍ ይቆርጡ ሰንድ አዘዘ ድል አድራጊ ጊዮርጊሲም እጂግ ደስ አለው እሳት ከሰማይ አውርዶ ሰባውን ነገስታት ያቃጥላቸው ዘንድ መከራውም ከክርስቲያን ወገን ጸጥ ይል ዘንድ ጌታችንን ለመነው ወዲያው እሳት ከሰማይ ወርዶ ከነሰራዊታቸው ጋር ሰባውን ነገስታት አቃጠላቸው ከዚም በሁአል የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተገልጾ ብዙ ቃል ኪዳን ሰጠው በምድር መታሰቢያህን የሚያደርጉ ሁሉ እኔ ሃጥያቱን ሁሉ ደመሣለው በመከራም ውስጥ ሆኖ በባህርም ሆነ በየብስ,ወይም በደዌ በስምህ የሚለምነኝን እኔ ፈጥኜ ከመከራው አድነዋለው ይህንንም ጌታችን ተናግሮ በክብር ወደ ሰማይ ወጣ ከዚ በሁአላ ከ7አመት ተጋድሎ በሁአላ ሚያዚያ 23 ቀን ራሱን ዘንበል አድሪጎ በሰይፍ ቆረጡት በመንግስተ ሰማያት አክሊላትን ተቀበለ ከአገልጋዮቹም የቀሩት ሲጋውን ወስደው በልብስ ጠቀለሉት ወደ ሃገሩም ልዳም ወሰዱት ቤተ ክርስቲያንም ሰርተው በውስጡአ አኖሩት ከርሱም ቁጥር የሌላቸው ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶች ተገለጠ ለእግዚአብሄርም ምስጋና ይሁን የቅዱስ ጊዮርጊሲም በረከቱ ረድኤቱ ሃገራችን ኢትዮጵያን እና ህዝቦቹአን ከስጋና ከነፍስ መከራ ይጠብቅልን!!!!!...................ቸር ያቆየን!

Thursday, April 15, 2010

አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ

የአባታችን የእስትንፋሰ ክርስቶስ የተወለዱበት ቦታ ዳውንት ፀውን ዓባይ ይባላል:በሰሜን በኩል የእናታቸው ሃገር ደብረ ድባ የቄርሎስ ቦታ ይባላል:የአባታቸውም ሃገር የእግዚአብሄር አብ ደብር አጠገብ ዳውንት(ደብረ አስጋጅ)ይባላል:የአባታቸውም ስም መልዓከ ምክሩ ሲባሉ እናታቸው ደግሞ ወለተ ማርያም ይባላሉ:እነዚ ባል እና ሚስት በህግ ጸንተው የሚኖሩ እንደ ዘካሪያስ እና እንደ ኤልሳቤጥ መልካም ስራን በመስራት እግዚአብሄርን የሚያገለግሉ ነበሩ:ቀድመውም 2 ልጆችን ወልደው ነበር እና ከዛም እመቤታችንን የተባረከ እግዚአብሄርን የሚያገለግል በጸሎቱ ሰውን የሚጠቅም ልጅ እንድትሰጣቸው ዘወትር ይለምኑአት ነበር: እግዚአብሄርም ፀሎታቸውን ሰምቶ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ሚያዚያ 8 ተፀነሱ እና ታህሳስ 8 ቀን ተወለዱ:ልክ በተወለዱ እለትም ተነስተው በግራቸው ቆመው 3 ግዜ ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስቅዱስ ብለው አመሰገኑ:9 ግዜም ሰግዱ:ከዚህም በሁአላ በ40 ቀናቸው ጥምቀትን ተጠምቀው ስማቸውም እስትንፋሰ ክርስቶስ ተባለ:ከዛም ቅዱስ ሚካኤል እየጠበቃቸው አደጉና አባትየው ዋሻ ውስጥ 60 አመት ወደ ኖረ ቅዱስ ኪራኮስ ወደ ሚባል አባት ወሰደው ትምህርት እንዲያስተምረው ለመኑት:ከዛም ፃድቁ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ በአባ ኪራኮስ ተመርቆ ትምህርቱን ጀመረና እንደሌላው ሰው ጊዜ አልፈጀበትም:ወዲአው ይረዳ ነበር ከዛም ፃድቁ አባታችን የተለያዩ የሃይማኖት ትምህርቶችን በፍጥነት ተማረ ከዛም በክርስቶስ ፍቅር በእመቤታችን ፍቅር ልቡ ደማ:በውስጥ በአፍአ ድንግል ስትሆን የህያው የእግዚአብሄር አብ የባህርይ ልጅ ወልድን በጡቶቹአ ወተት አጥብታ ያሳደገችው በሁለት ወገን ድንግል የምትሆን መልካሚቱአ እርግብ እመቤታችን ጽጌ የሚባል ልጁአን እንደምትስም እንዲሁ ጻድቁ አባታችንን ትስመው ነበር:ከዛም አባታችን በመንፈሳዊ ተጋድሎ ቅኑት እንደገበሬ ፅሙድ እንደበሬ ሆኖ ሳይመነኩስ የምንኩስናን ስራ መስራት ጀመረ:እንደ እሳት ወላፈን ፈጥኖ የሚያልፍ የዚን አለም ጣዕም በመናቅ ህሊናው እንደ እሳት ነደደ አንደበቱም 46ቱን ብሉያትን 35ቱን ሃዲሳትን መጽሃፍ አንባቢ አደረገው ከዚህም ሌላ ቅዱሳት መጽሃፍትን:-150ውን መዝሙረ ዳዊት,ድርሳናትን ውዳሴ ማርያምን,የጻድቃን እና የሰማእታትን መልክአ,አስራ ስምንቱን ተአምረ ማርያም,ተአምረ እየሱስ,የሰኔ ጎሎጎታ,ልፋፈ ጽድቅ,እቀበኒ ክርስቶስ,7ቱ ኪዳናትን,ባርቶስ,እና ገድለ አቡነ ኪሮስ,ጊዮርጊስ,ኤዎስጣቴዎስ,ገብረ መንፈስቅዱስ,ተሰአቱ ቅዱሳን እንዲሁም ሰይፈ ሲላሴን እና ሰይፈ መለኮትን እንዲሁም ሌሎችን ቅዱሳን መጽሃፍቶችን ዘወትር አብዝቶ ይፀልይ ነበር:ጻድቁ አባታችን ጾምና ጸሎትን ትዕግስት አርምሞ ልጉአም ሆኑለት:እግሮቹ በሐዋርያት ወንጌል ጭንጫ ላይ ቆሙ:ቅድስት ንጽህት ድንግል በምትሆን በእመቤታችን በማርያም ፍቅር ገመድ ተጎተተ:የአሸናፊ የእግዚአብሄር ስሙን በመፍራት ሰውነቱን ይገስጻል:በጻድቃን እና በሰማእታት ጎዳና ሰውነቱን ያሮጠዋል:ከዛም አባ ኪራኮስ አባታችንን መርቆ ወደ አባቱ ሰደደው:ከዛም አባትየው ስሙ ማርቆስ ወደሚባል ጳጳስ ክህነት ይሰጠው ዘንድ ወሰደው ከዛም ጳጳሱ ባርኮ ዲቁና ሾመው እና ወደ ሃገራቸው ዳውንት ተመለሱ:ከዛም በእመቤታችን እና በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በድቁና ያገለግል ጀመር አባቱን እና እናቱንም በማገልገል እስከ 14 አመቱ ድረስ ተቀመጠ በሁአላም በ 14 አመቱ አለምን ንቆ ይመንን ዘንድ ለቤተሰቦቹ ነገራቸው አባቱም ቤተ ክርስቲያን ሄዶ አልቅሶ ቢጸልይ "ይመነኩስ ዘንድ ይሂድ ስልጣኑ እስከ ሰማይ ከፍ ከፍ ይላል ስም አጠራሩ እስከ አለም ዳርቻ ይደርሳል"የሚል ቃል ከሰማይ ሰማና በፍቅርና በሰላም አሰናበቱት:ከዛም አባታችን በ14 አመቱ ብዙ ገዳማትን እየጎበኘ ወደ ደብረ ሃይቅ አቡነ ኢየሱስ ሞአ ደረሰ:ከዛም እንደገዳም ስርአት 3 አመት ተፈተነና ከዛም ምንኩስናን ለበሰ ከዛም ከብዙ ተጋድሎ በሁአላ ድቁና ወደ ሾመው ጳጳስ ሄዶ ቅስናን ተቀበለ ከጥቂት ቀንም በሁአላ ቁምስናን እና ኤጲስቆጶስነትንም ሾመው:ከዛም አባታችን "ጌታችን ሰውነቱን በገራህተ መስቀል የጣለ ነፍሱን ያገኛታል:ስለኔ ሰውነቱን በገራህተ መስቀል ይጣል"ያለውን አስቦ በጾም በጸሎት በትርህምት በስግደት ኖረ:ከዛም እንደ 12 ሃዋርያት አጋንንትን እያወጣ:ድውያንን ይፈውስ ለምጻምን ያነጻ ጀመር:ከዛም የአባታችን ተአምር በምድረ ኢትዮጵያ ተሰማ ህዝቡም እሱን ያይ ዘንድ ካለበት ይመጣል:ከዛም አባታችን ኢትዮጵያን እየተዘዋወረ ያስተምር ይጸልይ ጀመር በሁአላም በ33 አመቱ ወደ ደብረ ድባ መቶ ሚያዚያ 9 ቀን ምንኩስናን ተቀበለ በዚያች ቀንም አስኬማን,ቅናትን,ቀሚስን,መታጠቂያን,መስቀልን,በትርን ጭራንና ስእልን ተቀብሎ ሲጸልይ ዋለ:ከዛም እንዳስለመደው በየ ሃገሩ እየተዘዋወረ እያስተማረና ድውይን እየፈወሰ ሃገሪቱአን አቀና በየግዜውም የሚነሱ ንጉሶች ይመጡና ከአባታችን ዘንድ ይባረኩ ነበር:ብዙ ልጆችም አፍርቶ ነበር በስተመጨረሻም ጌታችን ከእናቱ እና ከብዙ ቅዱሳን ጋር ሆኖ ወደ አባታችን መቶ ብዙ ቃል ኪዳን ሰቱአቸዋል በስተመጨረሻም አባታችን አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ በ ሚያዚያ 9 ቀን አርፉ:: የአባታችን የአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ረድኤት እና በረከት አይለየን አሜን!!!!! ምንጭ ገድለ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ

Monday, April 12, 2010

ቅድስት እንባመሪና

የቅድስት እንባመሪና እናት ማርያም ትባላለች ገናም ህጻን እያለች ነበር በሞት የተለየቻት ከዛም አባቱአ ለአቅመ ሄዋን እስክትደርስ ድረስ በጎ ትምህርቶችን ሲያስተምራት አሳደጋት በሁአላም ለአቅመ ሄዋን ስደርስ አጋብቱአት እሱ ወደ መነኮሳት መኖሪያ ሄዶ ሊኖር እንደወደደ ሲነግራት እጂግ አልቅሳ "አባቴ ያንተን ነፍስ አድነህ የኔን ነፍስ ማጥፋት እንደት ይሆንልሃል ?" አለችውና አባቱአም እኔ የምሄደው ወደ ወንድ መነኮሳት ነው አንቺን ደግሞ ሴት ነሽ አያስገቡሽም ሲላት እንደወንድ ሱሪ አድርጌ ጸጉሬን ተቆርጬ ወንድ መስዬ ካንተ ጋር ሄዳለው አለችውና :ያላቸውን ንብረት ሁሉ ሽጠው እና ለደሃ መጽውተው ተያይዘው ገዳም ይገባሉ:: በዚአም ገዳም እጅግ እየተጋደሉ ኖሩ በሁአላም አባቱአ በጸና ታመመና አበ ምኔቱን አስጠርቶ ልጄን አደራ በምንም መልኩ ከገዳም እንዳይወጣብኝ ይልና አበ ምኔቱን አደራ ይለውና ያርፋል: ቅድስት እንባመሪናም ተጋድሎዋን ከቀድሞ እጅግ አብዝታ ትተጋ ጀመር:ከረጅም ግዜ በሁአላም የገዳሙ መነኮሳት ይሄ መነኩሴ ከኛ ጋር ለምንድን ነው ከገዳም ውጪ ለተልኮ የማይወጣው እያሉ አበ ምኔቱን አስጨነቁት በሁአላም አበ ምኔቱ ከመነኮሳቱ ጋር አብሮ ይሰዳት ጀመር የሚሄዱትም የገዳሙን ምግብ በየግዜው ከሚሰበስብላቸው አንድ ሰውዬ ቤት ነበር:እንዳስለመዱት በየግዜው ሲሄዱ አንድ ቀን ምግቡን የሚሰጣቸው ሰውዬ አንዲት ልጅ አለችውና ጎረቤት የሆነ አንድ ጎረምሳ ተደብቆ ይገባና የሰውዬውን ልጅ ድንግልናዋን ያፈርሳል በሁአላም አባትሽ ማነው እንዲ ያደረገሽ ብሎ ከጠየቀሽ እንባመሪና ነው በይ ይላታል:በሁአላም ጊዜ ይሄድና ልጅቱአ ታረግዛለች በሁአላም አባትየው ከማን እንዳረገዘች ሲጠይቃት ከመነኩሴው ከእንባመሪና ነው አለችው:ከዛም ያ ሰውዬ ወደ ገዳሙ ይመጣና ባአደባባይ መነኮሳቱን ይረግማቸው ጀመር ከዛ አበ ምኔቱ መጣና ምን ሆነህ ነው ቢለው ልጄን ያንተ መነኩሴ ደፍረብኝ ሲለው ታድያ ባንድ ሰው ጥፋት እነዚን ሁሉ ቅዱሳን ለምን በአደባባይ ትረግማለህ አለውና እንባመሪናን አስጠራት:መጣችና አቤት አባቴ ስትል ሁሉም ይሰድቡአት ጀመር ለምን እንደሚሰድቡአት ባታቅም ሴጣን የሰራባት ነገር እንዳለ ገብቱአት ዝም አለች በሁአላም ነገሩን ነገሩአት እና አበ ምኔቱ "እንባመሪና ይህ የመነኩሴ አይደለም የአለማውያን ባህሪ አይደለም የሴጣን እንጂ ይህን ለምን አደረክ?"ብሎ ቢጠይቃት እሱአም አባቴ ይቅር በለኝ ወጣትነት አታሎኝ ነው አባቴ ይቅር በለኝ ብላ አበ ምኔቱ እግር ስር ወደቀች በሁአላም አበ ምኔቱ ከገዳሙ አባረራት እና ከገዳሙ ውጪ ሆና ትጋደል ጀመር ያቺም ልጅ ስትወልድ አባቱአ ልጁን አምጥቶ ለእንባመሪና ሰጣት እንባመሪናም ለልጁ የሚሆን ወተት እና ምግብ በአካባቢው ያሉትን እረኞች እየለመነች አሳደገችው:ከ3 አመት በሁአላም መነኮሳቱ አበ ምኔቱን ለመኑት ባይሆን ከባድ ቀኖና ይሰጠውና ወደ ገዳም ይግባ አሉት:አበ ምኔቱም ልመናቸውን ተቀብሎ ከባድ ቀኖና ሰጣት እና ስጨርስ ወደ ገዳሙ ተቀላቀለች ከዛም ገዳሙ ውስጥ ያሉትን ከባድ ስራዎች ያሰራት ጀመር ከዛም በሁአላ ገዳም ውስጥ ጭንቅ የሆኑ ስራዎችን ያሰሩአት ጀመር የመነኮሳቱን ቤት ጠርጋ ተሸክማ ወስዳ ከገዳም ውጪ አውጥታ ትጥላለች:ያም የተወለደ ልጅ አድጎ እዛው መነኮሰ 40 አመትም ከተፈጸመ በሁአላ ቅድስት እንባመሪና 3ቀን ታማ አረፈች:ከዛም የገዳሙ መነኮሳት ተሰብስበው ደውል ደውለው ተሰበሰቡ ሊገንዙአትም ፈልገው ልብሱአን ሲያዎልቁት ሴት ሆና ሲያገኙአት እጅግ አዝነው አበ ምኔቱን አስጠሩት:አበ ምኔቱም የተፈጠረውን አይቶ እጅግ አዝኖ አለቀሰ ያለበደሉአ የሰጣትን ቅኖና እና የተናገራትን ተግሳጽ እያሰበ አምሪሮ ያለቅስ ጀመር:ከዛም ያን የልጅቱአ አባት አስጠርቶ የሆነውን ሁሉ ነገረው ከዛም በድኑአን ተሸክመው አበቱ ይቅር በለኝ እያሉ ዋሉ ማምሻውን ላይ የቅድስት እንባመሪና አስክሬን "እግዚአብሄር ይቅር ይበላቹ" ሲላቸው አውርደዋት በታላቅ ክብር ከስጋዋም ተባርከው ቀበሩአት ከመቃብሩአም እጅግ ብዙ የሆነ ድንቆች ተአምራት ተደረጉ ለእግዚአብሄር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚች ጻድቅ ጸሎት ይማረን:የቅድስት እንባመሪና በረከት አይለየን አሜን.......ቸር ያቆየን!!!!!ምንጭ መጽሃፈ ስንክሳር ነሃሴ 15

Saturday, April 10, 2010

ቅድስት ማርያም ግብጻዊት

የኢየሩሳሌም ሊቀፓፓስ ሳፍሮኒዮስ እንደጻፈው:- ቅድስት ማርያም ግብጻዊት የተወለደችው በግብጽ ሲሆን ገና የ12 አመት ልጅ እያለች ነበር ወደ እስክንድርያ በመሄድ ድንግልናዋን ያፈረሰችው:ከዚያም የዝሙት ፍቅር አድርባት:ለ17 አመት ያህል ሰዎችን በሚያቃጥል የሃጥያት እሳት ታስፈጃቸው ነበር ዝሙት እያሰራች:ብዙዎችንም ታስት ነበር:ዝሙት ከመውደድ የተነሳ ገንዝብ እንኩአን ልስጥሽ ሲሉ አትቀበልም ነበር:በእግዚአብሄርም አታምንም ነበር በዛው ፋንታ እንደፈለገች ትሆን ነበር:በልቡአ ከዚ ሲራዬ ማንም አይከለክለኝም ትል ነበር::አንድ ቀን ሊቢያውያን እና ግብጻውያን ወደ ባህር እየተቻኮሉ ሲሄዱ አይታ ወዴት እንደሚሄዱ ብጠይቃቸው የከበረ የጌታችንን መስቀል በዓል ለማክበር ወደ እየሩሳሌም እንደሚሄዱ ሲነግሩአት እና የሚሄደው ሰው ብዙ መሆኑን ሲታይ: ብዙ ዘመዶችን አገኛለው ብላ ከነሱ ጋር ለመሄድ ተነሳች:ለጉዞዋ ወይም ለምግብ የሚሆን አንድም ገንዘብ አልያዘችም ነበር:በሁአላም በሰውነቱአ ማማር ብዙዎችን በዝሙት ምክንያት አጠመደች ወደ ተቀደሰ ቦታ የሚሄዱቱን ሰዎች በማሳት ዋና የሰይጣን መረብ ሆና ነበር:በዚህም ስራዋ እየተኩራራች ለሰው ሁሉ ትናገር ነበር:የሃጥያተኛን ሞት የማይወድ እግዚአብሄር መመለሱአን እየጠበቀ ይታገሳት ነበር:በመጨረሻም እየሩሳሌም ደርሰው ከበዓሉ በፊት እንደለመደችው እንደውም በከፋ መልኩ ዝሙትን አብዝታ ትሰራ እና ሰውንም ታስት ነበር:የበዓሉ ዕለት ጠዋት ብዙ ተሳላሚዎች ጌታችን መቃብር ላይ ወደ ተሰራችው ቤተ-ክርስቲያን ሊሳለሙ ሲሄዱ አየችና እዛ ሄደው ምን እንደሚያደርጉ ለማወቅ ፊላጎት አደረባት እናም ህዝቡ በሚገቡበት በር እየተጋፋች ለመግባት ትሞክር ጀመር በሁአላም በሩ ጋር ስትደርስ የሆነ ሃይል ሲገፋት ይታወቃት ጀመር ለሎቹን ሰዎች ስታይ በቀላሉ ይገባሉ እና መጀመሪያ ላይ ምንድን ነው እያለች ትስቅ ነበር ደጋግማ ስትሞክር አልቻለችም በሁአላም ዝም ብላ በሩ ላይ ቆመች እንደገናም ደጋግማ ሞከረች በሁአላም ሲደክማት ግዜ እልፍ ብላ ከበሩ አጠገብ ቆመች በህሊናዋም በብዙ መከራ ምን እንደሆነ ታስብ ጀመር: ቅዱስ መስቀሉን ለማየት እሱአ ያልቻለችበትን ምክኒያት ታስብ ጀመር:የድህነት ቃል የልቦናዋን አይኖች ነካቸው እና እንዳልገባ የከለከለኝ የራሱአ የግል ሃጥያት መሆኑን ተረዳች:በሁአላም በማልቀስ እና ደረቱአን እየደቃች ከውስጣዊ ልቡአ ማዘን ጀመረች:"ለምን አልገባም? እንዳልገባ የከለከለኝ የኃጢአቴ ብዛት ነው?" እያለች ደጋግማ እራሱአን ትጠይቅ ጀመር:ያን ግዜ የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማሪያምን ስዕል ከበሩ ላይ አየችና ሄዳ ስዕሉአ ፊት ቆማ የስዕሉአን ግርማና ውበት ባየች ግዜ ያለፈ የራሱአ ሃጥያት ወለል ብሎ ታያት እና አፈረች በሁአላም በብዙ ለቅሶ ስዕሉአ ስር ወድቃ "ከንግዲ በሁአላ ጌታየን አገለግል እና ያንቺ ባርያ እሆን ዘንድ እድል አገኝ ይሆን ?" እያለች ታለቅስ እና ትለምን ጀመር:ጌታችንንም ካለችበት ስቃይና መከራ እንዲያድናት እና በመንገዱ እንዲመራት ለመነችው:"ቅዱስ መስቀሉን ካየው በሁአላ አለም እና ደስታዋን እንደምክድ ቃል ገባለው" ብላ ቃል ገባች:ከጸለየችም በሁአላ የመተማመን ስሜት ተሰማትና ወደ መስቀሉ ቦታ ወደሚያስገባው ቦታ ሄደች ከዚያም ያለችግር ገባች በሁአላም መስቀሉ ጋር ደርሳ በመንቀጥቅጥ እና በብዙ እምባ ሳመች የእግዚአብሄርን ሚስጥር እና ንስሃን እንዴት እንደሚቀበል አየች:ከዚያም ወታ ቃል ወደ ገባችበት ወደ እመቤታችን ስዕል ጋር ሄዳ "የሃጥአንን ንሰሃ ባንቺ አማላጅነት የሚቀበል እግዚአብሄር የተመሰገነ ይሁን:የከበርሽ እመቤቴ ሆይ ኃጥእት እኔ ምን እላለው?"አለችና "አሁን የገባውትን ቃል እፈጽም ዘንድ ግዜው ነው እጄን ይዘሽ ወደ ንስሃ ምሪኝ" አለች:ያን ግዜ የእመቤታችን ስእል አፍ አውጥታ "ዮርዳኖስን ብትሻገሪ እረፍት ታገኛለሽ" አለቻት:ከዛም እመቤቴ ሆይ አትተዪኝ ብላ አለቀሰች እና ከዚያ ተነስታ ወደ በረሃው ጉዞ ጀመረች ከመንገዶኞቹም አንዱ እህቴ ሆይ እንኪ ብሎ 3 ሳንቲም ሰጣት እና በነሱ ለመንገዱአ የሚሆን ዳቦ ገዝታ እያለቀሰች ከከተማው ወጣች:መንገድ ላይም መሸባትና የዮሃነስ መጥምቅ ቤት-ክርስቲያን አግኝታ እዛው ስታለቅስ አደረች:ጠዋትም አስቀድሳ እመቤታችንንም አንቺ ተከተይኝ እያለች ጉዞዋን ጀመረች ጀልባም ፈልጋ ዮርዳኖስን ተሻገረች ከዚአም ወደ አንድ በረሃ ደረሰች:በዚአም እህልም ሰውም ሳታገኝ ለ47 አመታት እየተጋደለች ወደሱ የሚመለሱትን ከሚቀበል ፈጣሪ ጋር ኖረች: ከ47 አመትም በሁአላ ቅዱስ ዞሲማሲን አግኝታ ሲላሳለፈችው እና ስለነበራት ህይወት አጫወተችው:ከዛም ለመጀመሪያው 17 አመታት የነበረባትን ፈተና እንዲ አለችው ""አባት ዞሲማስ ሆይ 17 አመት በዚ በረሃ ከአራዊት ከክፉ ምኞት እና ከክፉ ህሊና ጋር ስታገል ኖርኩ:ያለፈ ህይወቴንና ያሳለፍኩትን ደስታ እያሰብኩ እፈተን ነበር:ከረሃብ እና ከውሃ ጥም እንዲሁም ከጸሃይ ሃሩር የተነሳ በጣም ተሰቃይቻለው: ብዙ ግዜ እታመምና ለሞት እደርስ ነበር:ጌታዬም እንዲረዳኝ እለምነው ነበር ህሊናየን መጀመሪያ ወደ ተቀበለችኝ እመቤቴም ስዕል እሄድና እማጸናት ነበር ከዛም በሁአላ በ4ቱ ማእዘን የሚያበራ ብርሃን አይ ነበር""እያለችና ሌላም ሌላም ትነግረው ነበር:ከዛም ቅድስት ማሪያም ግብጻዊት በብዙ ተጋድሎ ሰይጣንን ድል ነስታ ቅዱስ ዞሲማሲን በሚቀጥለው አመት ወደዚ በረሃ ስትመጣ የጌታችንን ቅዱስ ስጋውንና ክቡር ደሙን በእለተ "ፀሎተ-ሃሙስ" ይዘህልኝ በዮርዳኖስ ባህር ዳር እንገናኝ አለችው ና ተመልሳ ወደ በረሃው ገባች በአመቱን ቅዱስ ዞሲማስ ይዞላት መቶ የዮርዳኖስ ባህርን እየተራመደች ስትመጣ ግዜ አይቶ እግዚአብሄርን እያመሰገነ ቅዱስ ስጋውንና ክቡር ደሙን አቀበላት ከዚያም እንደገና ቅዱስ ዞሲማስን አሰናበተችውና በሚቀጥለው አመት እንዲመጣ ነገረችው በሁአላም በአመቱ ሲመጣ አጣት እና እጂግ አለቀሰ በሁአላም ፈልጎ ሬሳዋን አገኘውና ሲሙአን ባለማወቁ ሲጸጸት ጊዜ አንድ ብጣቂ ወረቀት አገኘና አነበባት "" አባት ዞሲማስ ሆይ በጸሎተ ሃሙስ ማታ ከቅዱስ ሚስጥር ከተቀበልኩ በሁአላ ወደ አምላኬ ሄጃለው የደካማይቱን የማርያምን ስጋ በዚ ቦታ ቅበረው ዓፈር ወደ ዓፈር ይመለስ ዘንድ:ስለ እኔም ጸልይልኝ "" በሁአላም ሲሙአን በማወቁ ደስ እያለው እዛው ቀበራት እና ወደ በአቱ ተመለሰ:ቅድስት ማርያም ግብጻዊት ያረፈችው በሚያዚያ 6,522ዓ.ም. ነው:: የዚች ጻድቅ ማርያም ግብጻዊት በረከት አይለየን አሜን.......ቸር ያቆየን!!!