Saturday, April 10, 2010

ቅድስት ማርያም ግብጻዊት

የኢየሩሳሌም ሊቀፓፓስ ሳፍሮኒዮስ እንደጻፈው:- ቅድስት ማርያም ግብጻዊት የተወለደችው በግብጽ ሲሆን ገና የ12 አመት ልጅ እያለች ነበር ወደ እስክንድርያ በመሄድ ድንግልናዋን ያፈረሰችው:ከዚያም የዝሙት ፍቅር አድርባት:ለ17 አመት ያህል ሰዎችን በሚያቃጥል የሃጥያት እሳት ታስፈጃቸው ነበር ዝሙት እያሰራች:ብዙዎችንም ታስት ነበር:ዝሙት ከመውደድ የተነሳ ገንዝብ እንኩአን ልስጥሽ ሲሉ አትቀበልም ነበር:በእግዚአብሄርም አታምንም ነበር በዛው ፋንታ እንደፈለገች ትሆን ነበር:በልቡአ ከዚ ሲራዬ ማንም አይከለክለኝም ትል ነበር::አንድ ቀን ሊቢያውያን እና ግብጻውያን ወደ ባህር እየተቻኮሉ ሲሄዱ አይታ ወዴት እንደሚሄዱ ብጠይቃቸው የከበረ የጌታችንን መስቀል በዓል ለማክበር ወደ እየሩሳሌም እንደሚሄዱ ሲነግሩአት እና የሚሄደው ሰው ብዙ መሆኑን ሲታይ: ብዙ ዘመዶችን አገኛለው ብላ ከነሱ ጋር ለመሄድ ተነሳች:ለጉዞዋ ወይም ለምግብ የሚሆን አንድም ገንዘብ አልያዘችም ነበር:በሁአላም በሰውነቱአ ማማር ብዙዎችን በዝሙት ምክንያት አጠመደች ወደ ተቀደሰ ቦታ የሚሄዱቱን ሰዎች በማሳት ዋና የሰይጣን መረብ ሆና ነበር:በዚህም ስራዋ እየተኩራራች ለሰው ሁሉ ትናገር ነበር:የሃጥያተኛን ሞት የማይወድ እግዚአብሄር መመለሱአን እየጠበቀ ይታገሳት ነበር:በመጨረሻም እየሩሳሌም ደርሰው ከበዓሉ በፊት እንደለመደችው እንደውም በከፋ መልኩ ዝሙትን አብዝታ ትሰራ እና ሰውንም ታስት ነበር:የበዓሉ ዕለት ጠዋት ብዙ ተሳላሚዎች ጌታችን መቃብር ላይ ወደ ተሰራችው ቤተ-ክርስቲያን ሊሳለሙ ሲሄዱ አየችና እዛ ሄደው ምን እንደሚያደርጉ ለማወቅ ፊላጎት አደረባት እናም ህዝቡ በሚገቡበት በር እየተጋፋች ለመግባት ትሞክር ጀመር በሁአላም በሩ ጋር ስትደርስ የሆነ ሃይል ሲገፋት ይታወቃት ጀመር ለሎቹን ሰዎች ስታይ በቀላሉ ይገባሉ እና መጀመሪያ ላይ ምንድን ነው እያለች ትስቅ ነበር ደጋግማ ስትሞክር አልቻለችም በሁአላም ዝም ብላ በሩ ላይ ቆመች እንደገናም ደጋግማ ሞከረች በሁአላም ሲደክማት ግዜ እልፍ ብላ ከበሩ አጠገብ ቆመች በህሊናዋም በብዙ መከራ ምን እንደሆነ ታስብ ጀመር: ቅዱስ መስቀሉን ለማየት እሱአ ያልቻለችበትን ምክኒያት ታስብ ጀመር:የድህነት ቃል የልቦናዋን አይኖች ነካቸው እና እንዳልገባ የከለከለኝ የራሱአ የግል ሃጥያት መሆኑን ተረዳች:በሁአላም በማልቀስ እና ደረቱአን እየደቃች ከውስጣዊ ልቡአ ማዘን ጀመረች:"ለምን አልገባም? እንዳልገባ የከለከለኝ የኃጢአቴ ብዛት ነው?" እያለች ደጋግማ እራሱአን ትጠይቅ ጀመር:ያን ግዜ የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማሪያምን ስዕል ከበሩ ላይ አየችና ሄዳ ስዕሉአ ፊት ቆማ የስዕሉአን ግርማና ውበት ባየች ግዜ ያለፈ የራሱአ ሃጥያት ወለል ብሎ ታያት እና አፈረች በሁአላም በብዙ ለቅሶ ስዕሉአ ስር ወድቃ "ከንግዲ በሁአላ ጌታየን አገለግል እና ያንቺ ባርያ እሆን ዘንድ እድል አገኝ ይሆን ?" እያለች ታለቅስ እና ትለምን ጀመር:ጌታችንንም ካለችበት ስቃይና መከራ እንዲያድናት እና በመንገዱ እንዲመራት ለመነችው:"ቅዱስ መስቀሉን ካየው በሁአላ አለም እና ደስታዋን እንደምክድ ቃል ገባለው" ብላ ቃል ገባች:ከጸለየችም በሁአላ የመተማመን ስሜት ተሰማትና ወደ መስቀሉ ቦታ ወደሚያስገባው ቦታ ሄደች ከዚያም ያለችግር ገባች በሁአላም መስቀሉ ጋር ደርሳ በመንቀጥቅጥ እና በብዙ እምባ ሳመች የእግዚአብሄርን ሚስጥር እና ንስሃን እንዴት እንደሚቀበል አየች:ከዚያም ወታ ቃል ወደ ገባችበት ወደ እመቤታችን ስዕል ጋር ሄዳ "የሃጥአንን ንሰሃ ባንቺ አማላጅነት የሚቀበል እግዚአብሄር የተመሰገነ ይሁን:የከበርሽ እመቤቴ ሆይ ኃጥእት እኔ ምን እላለው?"አለችና "አሁን የገባውትን ቃል እፈጽም ዘንድ ግዜው ነው እጄን ይዘሽ ወደ ንስሃ ምሪኝ" አለች:ያን ግዜ የእመቤታችን ስእል አፍ አውጥታ "ዮርዳኖስን ብትሻገሪ እረፍት ታገኛለሽ" አለቻት:ከዛም እመቤቴ ሆይ አትተዪኝ ብላ አለቀሰች እና ከዚያ ተነስታ ወደ በረሃው ጉዞ ጀመረች ከመንገዶኞቹም አንዱ እህቴ ሆይ እንኪ ብሎ 3 ሳንቲም ሰጣት እና በነሱ ለመንገዱአ የሚሆን ዳቦ ገዝታ እያለቀሰች ከከተማው ወጣች:መንገድ ላይም መሸባትና የዮሃነስ መጥምቅ ቤት-ክርስቲያን አግኝታ እዛው ስታለቅስ አደረች:ጠዋትም አስቀድሳ እመቤታችንንም አንቺ ተከተይኝ እያለች ጉዞዋን ጀመረች ጀልባም ፈልጋ ዮርዳኖስን ተሻገረች ከዚአም ወደ አንድ በረሃ ደረሰች:በዚአም እህልም ሰውም ሳታገኝ ለ47 አመታት እየተጋደለች ወደሱ የሚመለሱትን ከሚቀበል ፈጣሪ ጋር ኖረች: ከ47 አመትም በሁአላ ቅዱስ ዞሲማሲን አግኝታ ሲላሳለፈችው እና ስለነበራት ህይወት አጫወተችው:ከዛም ለመጀመሪያው 17 አመታት የነበረባትን ፈተና እንዲ አለችው ""አባት ዞሲማስ ሆይ 17 አመት በዚ በረሃ ከአራዊት ከክፉ ምኞት እና ከክፉ ህሊና ጋር ስታገል ኖርኩ:ያለፈ ህይወቴንና ያሳለፍኩትን ደስታ እያሰብኩ እፈተን ነበር:ከረሃብ እና ከውሃ ጥም እንዲሁም ከጸሃይ ሃሩር የተነሳ በጣም ተሰቃይቻለው: ብዙ ግዜ እታመምና ለሞት እደርስ ነበር:ጌታዬም እንዲረዳኝ እለምነው ነበር ህሊናየን መጀመሪያ ወደ ተቀበለችኝ እመቤቴም ስዕል እሄድና እማጸናት ነበር ከዛም በሁአላ በ4ቱ ማእዘን የሚያበራ ብርሃን አይ ነበር""እያለችና ሌላም ሌላም ትነግረው ነበር:ከዛም ቅድስት ማሪያም ግብጻዊት በብዙ ተጋድሎ ሰይጣንን ድል ነስታ ቅዱስ ዞሲማሲን በሚቀጥለው አመት ወደዚ በረሃ ስትመጣ የጌታችንን ቅዱስ ስጋውንና ክቡር ደሙን በእለተ "ፀሎተ-ሃሙስ" ይዘህልኝ በዮርዳኖስ ባህር ዳር እንገናኝ አለችው ና ተመልሳ ወደ በረሃው ገባች በአመቱን ቅዱስ ዞሲማስ ይዞላት መቶ የዮርዳኖስ ባህርን እየተራመደች ስትመጣ ግዜ አይቶ እግዚአብሄርን እያመሰገነ ቅዱስ ስጋውንና ክቡር ደሙን አቀበላት ከዚያም እንደገና ቅዱስ ዞሲማስን አሰናበተችውና በሚቀጥለው አመት እንዲመጣ ነገረችው በሁአላም በአመቱ ሲመጣ አጣት እና እጂግ አለቀሰ በሁአላም ፈልጎ ሬሳዋን አገኘውና ሲሙአን ባለማወቁ ሲጸጸት ጊዜ አንድ ብጣቂ ወረቀት አገኘና አነበባት "" አባት ዞሲማስ ሆይ በጸሎተ ሃሙስ ማታ ከቅዱስ ሚስጥር ከተቀበልኩ በሁአላ ወደ አምላኬ ሄጃለው የደካማይቱን የማርያምን ስጋ በዚ ቦታ ቅበረው ዓፈር ወደ ዓፈር ይመለስ ዘንድ:ስለ እኔም ጸልይልኝ "" በሁአላም ሲሙአን በማወቁ ደስ እያለው እዛው ቀበራት እና ወደ በአቱ ተመለሰ:ቅድስት ማርያም ግብጻዊት ያረፈችው በሚያዚያ 6,522ዓ.ም. ነው:: የዚች ጻድቅ ማርያም ግብጻዊት በረከት አይለየን አሜን.......ቸር ያቆየን!!!

No comments:

Post a Comment