Monday, April 12, 2010

ቅድስት እንባመሪና

የቅድስት እንባመሪና እናት ማርያም ትባላለች ገናም ህጻን እያለች ነበር በሞት የተለየቻት ከዛም አባቱአ ለአቅመ ሄዋን እስክትደርስ ድረስ በጎ ትምህርቶችን ሲያስተምራት አሳደጋት በሁአላም ለአቅመ ሄዋን ስደርስ አጋብቱአት እሱ ወደ መነኮሳት መኖሪያ ሄዶ ሊኖር እንደወደደ ሲነግራት እጂግ አልቅሳ "አባቴ ያንተን ነፍስ አድነህ የኔን ነፍስ ማጥፋት እንደት ይሆንልሃል ?" አለችውና አባቱአም እኔ የምሄደው ወደ ወንድ መነኮሳት ነው አንቺን ደግሞ ሴት ነሽ አያስገቡሽም ሲላት እንደወንድ ሱሪ አድርጌ ጸጉሬን ተቆርጬ ወንድ መስዬ ካንተ ጋር ሄዳለው አለችውና :ያላቸውን ንብረት ሁሉ ሽጠው እና ለደሃ መጽውተው ተያይዘው ገዳም ይገባሉ:: በዚአም ገዳም እጅግ እየተጋደሉ ኖሩ በሁአላም አባቱአ በጸና ታመመና አበ ምኔቱን አስጠርቶ ልጄን አደራ በምንም መልኩ ከገዳም እንዳይወጣብኝ ይልና አበ ምኔቱን አደራ ይለውና ያርፋል: ቅድስት እንባመሪናም ተጋድሎዋን ከቀድሞ እጅግ አብዝታ ትተጋ ጀመር:ከረጅም ግዜ በሁአላም የገዳሙ መነኮሳት ይሄ መነኩሴ ከኛ ጋር ለምንድን ነው ከገዳም ውጪ ለተልኮ የማይወጣው እያሉ አበ ምኔቱን አስጨነቁት በሁአላም አበ ምኔቱ ከመነኮሳቱ ጋር አብሮ ይሰዳት ጀመር የሚሄዱትም የገዳሙን ምግብ በየግዜው ከሚሰበስብላቸው አንድ ሰውዬ ቤት ነበር:እንዳስለመዱት በየግዜው ሲሄዱ አንድ ቀን ምግቡን የሚሰጣቸው ሰውዬ አንዲት ልጅ አለችውና ጎረቤት የሆነ አንድ ጎረምሳ ተደብቆ ይገባና የሰውዬውን ልጅ ድንግልናዋን ያፈርሳል በሁአላም አባትሽ ማነው እንዲ ያደረገሽ ብሎ ከጠየቀሽ እንባመሪና ነው በይ ይላታል:በሁአላም ጊዜ ይሄድና ልጅቱአ ታረግዛለች በሁአላም አባትየው ከማን እንዳረገዘች ሲጠይቃት ከመነኩሴው ከእንባመሪና ነው አለችው:ከዛም ያ ሰውዬ ወደ ገዳሙ ይመጣና ባአደባባይ መነኮሳቱን ይረግማቸው ጀመር ከዛ አበ ምኔቱ መጣና ምን ሆነህ ነው ቢለው ልጄን ያንተ መነኩሴ ደፍረብኝ ሲለው ታድያ ባንድ ሰው ጥፋት እነዚን ሁሉ ቅዱሳን ለምን በአደባባይ ትረግማለህ አለውና እንባመሪናን አስጠራት:መጣችና አቤት አባቴ ስትል ሁሉም ይሰድቡአት ጀመር ለምን እንደሚሰድቡአት ባታቅም ሴጣን የሰራባት ነገር እንዳለ ገብቱአት ዝም አለች በሁአላም ነገሩን ነገሩአት እና አበ ምኔቱ "እንባመሪና ይህ የመነኩሴ አይደለም የአለማውያን ባህሪ አይደለም የሴጣን እንጂ ይህን ለምን አደረክ?"ብሎ ቢጠይቃት እሱአም አባቴ ይቅር በለኝ ወጣትነት አታሎኝ ነው አባቴ ይቅር በለኝ ብላ አበ ምኔቱ እግር ስር ወደቀች በሁአላም አበ ምኔቱ ከገዳሙ አባረራት እና ከገዳሙ ውጪ ሆና ትጋደል ጀመር ያቺም ልጅ ስትወልድ አባቱአ ልጁን አምጥቶ ለእንባመሪና ሰጣት እንባመሪናም ለልጁ የሚሆን ወተት እና ምግብ በአካባቢው ያሉትን እረኞች እየለመነች አሳደገችው:ከ3 አመት በሁአላም መነኮሳቱ አበ ምኔቱን ለመኑት ባይሆን ከባድ ቀኖና ይሰጠውና ወደ ገዳም ይግባ አሉት:አበ ምኔቱም ልመናቸውን ተቀብሎ ከባድ ቀኖና ሰጣት እና ስጨርስ ወደ ገዳሙ ተቀላቀለች ከዛም ገዳሙ ውስጥ ያሉትን ከባድ ስራዎች ያሰራት ጀመር ከዛም በሁአላ ገዳም ውስጥ ጭንቅ የሆኑ ስራዎችን ያሰሩአት ጀመር የመነኮሳቱን ቤት ጠርጋ ተሸክማ ወስዳ ከገዳም ውጪ አውጥታ ትጥላለች:ያም የተወለደ ልጅ አድጎ እዛው መነኮሰ 40 አመትም ከተፈጸመ በሁአላ ቅድስት እንባመሪና 3ቀን ታማ አረፈች:ከዛም የገዳሙ መነኮሳት ተሰብስበው ደውል ደውለው ተሰበሰቡ ሊገንዙአትም ፈልገው ልብሱአን ሲያዎልቁት ሴት ሆና ሲያገኙአት እጅግ አዝነው አበ ምኔቱን አስጠሩት:አበ ምኔቱም የተፈጠረውን አይቶ እጅግ አዝኖ አለቀሰ ያለበደሉአ የሰጣትን ቅኖና እና የተናገራትን ተግሳጽ እያሰበ አምሪሮ ያለቅስ ጀመር:ከዛም ያን የልጅቱአ አባት አስጠርቶ የሆነውን ሁሉ ነገረው ከዛም በድኑአን ተሸክመው አበቱ ይቅር በለኝ እያሉ ዋሉ ማምሻውን ላይ የቅድስት እንባመሪና አስክሬን "እግዚአብሄር ይቅር ይበላቹ" ሲላቸው አውርደዋት በታላቅ ክብር ከስጋዋም ተባርከው ቀበሩአት ከመቃብሩአም እጅግ ብዙ የሆነ ድንቆች ተአምራት ተደረጉ ለእግዚአብሄር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚች ጻድቅ ጸሎት ይማረን:የቅድስት እንባመሪና በረከት አይለየን አሜን.......ቸር ያቆየን!!!!!ምንጭ መጽሃፈ ስንክሳር ነሃሴ 15

No comments:

Post a Comment