Saturday, May 1, 2010

ተአምረ ጊዮርጊስ

ተአምረ ጊዮርስ 12ኛ ተአምር:- ፀሎቱና በረከቱ ልመናው ለሁላችን በእውነት ለዘላለሙ ይደረግልንና ቅዱስ ጊዮርጊስ ያደረገው ተአምር ይህ ነው:: በፍጹም ልቡ ቅዱስ ጊዮርጊስን የሚወድ በግብጽ ሃገር የሚኖር አንድ ሰው ነበረ ከፍቅሩም ብዛት የተነሳ እጅግ ያማረ ቤተ ክርስቲያን አሳነፀ:የእግዚአብሄርንም የህጉን ታቦት ለማስገባት በፈለገ ግዜ አንድ ከሃዲ ንጉስ መጣና ከሚስቱ ጋር ከቤተ ክርስቲያኑ ገብቶ መኖሪያውን በዚያ አደረገ:ሰውየውም በችኮላ ሄዶ ይህንን ነገር ለሊቀ ጳጳሱ ነገረው ሊቀ ጳጳሱም ተነስቶ ወደ ንጉሱ ሄደና ለምን የማይገባ ስራ ከቤተ ክርስቲያን ገብተህ ስለምን ትቀመጣለህ ቤተ ክርስቲያኒቱ የታነፀችው በሃያሉ በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም ነውና አለው::ንጉሱም ይህንን ንግግር ሰምቶ እጅግ ተቆጣና ያስረው ይገርፈውም ዘንድ ወደደ ሊቀ ጳጳሱም እጅግ አዘነና አይኖቹን ወደሰማይ አቅንቶ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሃያሉ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስን እንዲ ሲል አዳኘው:"ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ እኔ ሰማዕት ነኝ አትበል:በዚህ በአላዊ ንጉስ ላይ ሃይልህን የማትገልጽ ከሆነ ከማህበረ ሰማዕት ሁሉ ጋራ በእግዚአብሄር ፊት አትቁም":ሊቀ ጳጳሱም ይህንና የመሳሰለውንም ሁሉ እየተናገረ ሳለ ሃያሉ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ በግልጽ እያዩት በነጭ ፈረስ ተቀምጦ በሰማይ ላይ እንደ እሳት እያንበለበለ በድንገት ከተፍ ብሎ ወደ ከሃዲው ንጉስ ገባና በጦር ወግቶ ከዙፋኑ ገለበጠው ከቤተ ክርስቶያኑም ሩቅ በሆነ ቦታ ወስዶ በምድር ላይ ዘረረውና በዚያን ግዜ ክፉ ሞት ሞተ:ሚስቱም እንዲሁ:የሚንቀሳቀስና የማይንቀሳቀስ ንብረቱን ሁሉ በተነው ከቶ ምንም የተረፈ አልነበረም::በዚያም የነበሩ ሰዎች ሁሉ ታላቅ ፍርሃት ወደቀባችው ፈጽመውም አደነቁ ሊቀ ጳጳሱም ከተደረገው ተአምራት የተነሳ ደነገጠ ፈጽሞም አደነቀ:ከዚህም በሁአላ ሃያሉ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ጳጳሱን ከገዘትከኝ ግዝት ፍታኝ አለውና ፈታው::ነዚያን ግዜም በስሙ ከታነፀው ቤተ ክርስቲያን በፍጹም ደስታ በምስጋናና በዝማሬ በሃያሉ ሰማዕት በቅዱስ ጊዮርጊስ እጅ ሃይሉን የገለፀውን እግዚአብሄርን እያመሰገኑ ታቦተ ህጉን አስገቡ::ፀሎቱና በረከቱ አማላጅነቱ ለሁላችን በዕውነት ይደረግልን ለዘላለሙ አሜን!!!!!...........ቸር ያቆየን.

No comments:

Post a Comment