Saturday, May 15, 2010

የበረሃ አባቶች መልዕክት (ከገዳም የመጣ መልዕክት)

1:- ይድረስ ለኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች:-
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን:
በእግዚአብሄር ቸርነት: በእመቤታችን አማላጅነት: በመላእክት ተራዳይነት: በቅዱሳን ፀሎት: እስከዛሬ በህይወት ሳንጥፋ ላቆየን አምላክ ምስጋና ይግባውና ቀሪ ህይወታችንንም በሰላም በጤና በፍቅር ያቆየን ዘንድ የቸሩ ፈጣርያችን ቸርነት አይለየን እያልኩ ይህችን አጭር እና አብይ መልዕክት አስተላልፋለው እና እግዚአብሄር ቢፈቅድ ሁላችንም በአንድ ላይ ሆነን ለራሳችንም ፍጹም ሰላምን አግኝተን ለሌላው እንድንተርፍ እና ለሃገራችንም እግዚአብሄር ፍጹም ምህረቱን እንዲያወርድልን መንግስተ ሰማያትንም እንዲያወርሰን ሁላችንም ንስሃ እንግባ እላለው!!!!!!!
ንሰሃ ማለት:- ከእግዚአብሄር ጋር መታረቅ ማለት ነው:
ከእግዚአብሄር ጋር መታረቅ ማለት ከሃጥያት ርቆ የእግዚአብሄርን መንገድ ተከትሎ መሄድ ሲሆን: ንስሃ ለመግባት ደግሞ ከልጅነት እስከ እውቀት የሰራነውን ሃጥያት ወደ ካህናት ቀርበን ራሳችንን ገልጸን አንድም ሳናስቀር የበደልነውን ተናዘን ቀኖናችንን መውሰድ ነው:ከዛም የዕለት ኑሮዋችንን እግዚአብሄርን በማስቀደም ማከናወን የሚገባንን ማከናወን ነው::!!!!!!!
2:- ይድረስ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መንፈሳዊ ማህበሮች እና የጽዋ ማህበሮች:-
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን:
በእግዚአብሄር ቸርነት: በእመቤታችን አማላጅነት: በመላእክት ተራዳይነት: በቅዱሳን ፀሎት:የቤተ ክርስቲያናችን ማህበራት ዛሬ ላይ ደርሳቹ ለምዕመኑ የሃይሞኖትን ፍቅርን እና ጣዕምን እንዲያድርበት አልፎም ቤተ ክርስቲያኖቻችንን እንዲረዱ እንድታደርጉ ለረዳቹ እግዚአብሄር ምስጋና ይሁንና: የበለጠ ደግሞ እግዚአብሄር ፈቅዶ ምዕመኑን ንሰሃ እንዲገባ የበለጠ የእለት የእለት መልዕክታቹ እንዲሆን በእግዚአብሄር ስም እጠይቃለው: ሲጀመርም የመንፈሳዊ ማህበራት የመጀመሪያ አላማ ሰዉን ንሰሃ አስገብቶ በሃይማኖት አጽንቶ ፍጻሜ እንዲያምር ሲሆን ከዛ በመቀጠል ይሆናል እንግዲ ሌላው ሌላው መልእክት መተላለፍ ያለበት እና ሁላችንም ንሰሃ ገብተን እግዚአብሄርን ለመለመን ይርዳን !!!!!!!
3:- ይድረስ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ወንጌል ሰባክያን እና ዘማርያን:-
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን:
በእግዚአብሄር ቸርነት: በእመቤታችን አማላጅነት: በመላእክት ተራዳይነት: በቅዱሳን ፀሎት:የሃዋርያትን:የ72 አርድእትን የተለያዩ የቀደሙ ቅዱሳን አባቶችን ፈለግ ተከትላቹ ለምእመኑ የክርስቶስን ወንጌል እንድትሰብኩ እና ሰዉ በሙሉ ስለ አማናዊው ክርስቶስ እንዲያውቅ እንድታስተምሩ ለረዳችሁ ለእግዚአብሄር ምስጋና ይሁንና: የትኛውም ሰባኪያን ወይም መዘምራን የመጀመርያው አላማው ቤተክርስቲያናችንን ማገልገል ሲሆን ምእመኑንም ወደ ንሰሃ የመምራት ሃላፊነት አለበት:እናም ምእመኑን በተደጋጋሚ ንሰሃ ማስገባት:ስለ ንሰሃ መስበክ የመጀመርያ አርዕስታቹ እንዲሆን በቸሩ እግዚአብሄር ስም እጠይቃለው!!!!!!!
4:- ይድረስ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አባቶች:-
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን:
በእግዚአብሄር ቸርነት: በእመቤታችን አማላጅነት: በመላእክት ተራዳይነት: በቅዱሳን ፀሎት: ስልጣነ ሃዋርያትንም የያዛቹ አይንተ እግዚአብሄር ካህናት ለህዝበ ክርስቲያኑ እረኛ እንድትሆኑ ለራዳቹ ለእግዚአብሄር ምስጋና ይድረስና: ቸሩ ፈጣርያችን እግዚአብሄር እረኛ እንድትሆኑ አድርጎ የረዳችሁን አምላክን ለማገልገል ዘወትር የማትሰንፉ የክርስቶስ አይኖች እኔ ሳይገባኝ የምለምናቹ እውነተኛ እረኛ በጠፋበት በዚህ ሰአት ነገ ዛሬ ሳትሉ እውነተኛ እረኛ እንድትሆኑን ለልጆቻቹ ወደ ንሰሃ መቅረብን የተቻላችሁን እንድታደርጉል ዘወትር በምጠሩት በቸሩ እግዚአብሄር ስም እጠይቃለው !!!!!!!

ማጠቃለያ:- እግዚአብሄር አምላክ ህይወታችንን ሳይወስድ እድሜ ለንሰሃ እየሰጠን መሆኑን አውቀን ከሃጥያት ርቀን አባቶቻችን በተጓዙበት መንገድ ተጉዘን ህይወታችን አምሮ እና ሰምሮ ኋላም ፍጹም መንግስተሰማያትን ለመውረስ ነገ ዛሬ ሳንል ንስሃ እንግባ !!!!!!!
ይህንንም ጽሁፍ ማነው የጻፈው ከየት ነው የመጣው ከሚለው ምንድን ነው የሚለው ላይ አተኩረን እናንብብ:
ወስበሃት ለእግዚአብሄር
ወወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር!!!!!!!
እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ ህዝቦቿንም ይጠብቅልን!!!!

No comments:

Post a Comment