Sunday, May 2, 2010

አባ መቃርስ

አባ መቃርስ በግብጽ ደቡብ መኑፍ ከሚባል አውራጃ ሳሱይር ከሚባል መንደር ከሚኖሩ ሰዎች ወገን ነው:ወላጆቹም ደጎች እውነተኞች ነበሩ አባቱም አብርሃም እናቱም ሳራ ይባላሉ:እናቱም እንደ ኤልሳቤጥ እና ሳራ በእግዚአብሄር ትዛዝ ጸንታ የምትኖር ናት አባቱም በፈሪአ እግዚአብሄር ሆኖ ንጽህናውን እና ቅድስናውን ጠብቆ ሁል ግዜ ቤተ ክርስቲያንን በማግልገል ፀንቶ ይኖራል:እግዚአብሄርም በላያቸው በረከቱን አሳድሮ በስራቸው ሁሉ ከፍ ከፍ አደረጋቸው:ለድሆችም የሚመጸውቱ ለሰው ሁሉ የሚራሩ ናቸው:በፆም በፀሎት ተወስነው እንዲ ባለ ገድል ሲኖሩ ግን ልጅ አልነበራቸውም ለአብርሃምም በለሊት ራእይ ከእግዚአብሄር ዘንድ በልጅ አምሳል ተገለጠለት በአለም ሁሉ የሚታወቅ ብዙ መንፈሳውያን ልጆችን የሚወልድ ልጅን ይሰጠው ዘንድ እግዚአብሄር እንደወደደ ነገረው:ከዚም በሁአላ ይህ የከበረ ልጅ መቃርስን እግዚአብሄር ሰጠው ትርጉአመውም ብፁእ ማለት ነው በላዩም የእግዚአብሄር ፀጋ አደረበት:ለወላጆቹም ይታዘዝ እና ያገለግል ነበር ባደገ ግዜ ያጋቡትም ዘንድ አሰቡ እርሱ ግን ያን አይሻም ነበር ፈቃዳቸውን ይፈፅም ዘንድ ግድ ብለው አጋቡት:ወደ ሙሽራይቱም በገባ ግዜ ራሱን እንደታመመ ሰው አደረገ እንዲሁም ሆኖ ብዙ ቀን ኖረ:ከዚአም በሁአላ አባቱን ተወኝ ወደ ገዳም ልሂድ ከበሽታዬ ትንሽ ጤናን ባገኝ አለው:እግዚአብሄር ወደ ሚወደው ስራ ይመራው ዘንድ ሁል ግዜ በፆም እና በፀሎት ሆኖ ይለምነው ነበር:ከዚህም በሁአላ ወደ አስቀጥስ በረሃ ሄደ ከበረሃው በገባ ግዜ ራዕይን አየ:ስድስት ክንፍ ያለው ኪሩብ እጅና እግሩን ይዞ ወደ ተራራው ላይ እንደሚያወጣው እና የአስቀጥንስ በረሃ ምስራቁአን ምዕራቡአን የዚአችን በረሃ አራት መአዘኑአን አሳይቶ እነሆ ይችን በረሃ መላዋን ላንተ እና ለልጆችህ እርስት አድርጎ እግዚአብሄር ሰቶሃል አለው:ከበረሃውም በተመለሰ ግዜ ያቺ ብላተና ሚስቱ ታማ አገኛት ጥቂት ቆይታ በድንግልናዋ እንዳለች አረፈች:የክብር ባለቤት እግዚአብሄርን አመሰገነ:ከጥቂት ከኖች በሁአላ እናት አባቱም አረፉ:የተውለትንም ገንዘብ በሙሉ ለድሆች እና ለጦም አዳሪዎች ሰጠ:የሳሱይር ሰዎች ግን እውነተኛነቱን እና ቅድስናውን አይተው ቅስና አሾሙት:ከከተማውም ውጪ ቤት ሰሩለት ቅዱስ ስጋውን እና ክቡር ደሙን ይቀበሉ ዘንድ ወደ እሱ ይሄዱ ነበር:
በዚአች አገርም አንዲት ድንግል ብላቴና ነበረች ከአንድ ጎልማሳ ጋርም አመንዝራ ፀነሰች ጎልማሳውም አባትሽ ድንግልናሽን ማን አጠፋው ብሎ ሲጠይቅሽ መቃርስ የሚባለው ባህታዊ ቄስ እሱ ስለ ደፈረኝ ነው በይው ብሎ መከራት ፅንሱአም በታወቀ ግዜ አባቱአ ይህን አሳፋሪ ስራ ባንቺ ላይ የሰራብሽ ማነው ብሎ ጠየቃት:እሱአም በአንዲት ቀን መቃርስ ወደሚባለው ቄስ ሄጄ ሳለው በሃይል ይዞኝ ከኔ ጋር ተኛ እናም ከሱ ፀነስኩ ብላ መለሰችለት:ወላጆቹአም በሰሙ ግዜ እጅግ ተቆጡ ከብዙ ሰዎችም ጋራ ወደ ቅዱስ መቃርስ ሄደው ይዘው ከበአቱ አወጡት እሱ ግን ምን እንደሆነ አላወቀም ነበር:ለመሞት እስኪቃረብም አጽንተው ደበደቡት እሱም ሃጥያቴ ምንድን ናትና ነው እናንተ ያለ ርህራሄ ትደበድቡኛላቹና እያለ ይጠይቃቸው ነበር:ከዚህ በሁአላ በፍም የጠቆሩ ገሎችን ባንገቱ ላይ በገመድ አንጠልጥለው ወዲያ እና ወዲ እየጎተቱ የልጃችንን ድንግልና ያጠፋ ይህ ነው እያሉ እንደ እብድ በላዩ ይጮሁ ጀመር:የዚያን ግዜ መላዕክት እንደሰው ተገልጠው የሚያሰቃዩትን ሰዎች ይህ ተጋዳይ ምን አደረገ አሉአቸው እነሱም በልጃቸው ላይ የሃፍረትን ስራ እንደሰራ አድርገው መልሰው ነገሩአቸው እነዚያ መላዕክትም ይህ ነገር ሃሰት ነው እኛ ይህን ሰው ከታናሽነቱ ጀምሮ እንከዚ ቀን እናውቀዋለን:እሱ የተመረጠ ፃድቅ ሰው ነውና አሉአቸው:የታሰረበትንም ፈተው ከላዩ ላይ ገሎቹን ጣሉ እነዚያ ክፉዎች ግን ዋስ እስከሚሰጠን ድረስ አንለቀውም አሉ እጅ ስራውን የሚሸጥለት አንድ ሰው መጣ ለልጅቱአም በየግዜው ምግቡአን ሊሰጣት ዋስ ሆነው ከዚያ በሁአላ አሰናብተው ወደ በአቱ ተመልሶ ገባ ከዚያች ቀን ጀምሮ ራሱን በራሱ መቃርስ ሆይ"እነሆ እንግዲ ባለ ሚስት እና ባለ ልጅ ሆነሃል ለሊት እና ቀን መስራት ይገባሃል" እያለ ያቺ ሃሰተኛ ልጅ የምትወልድበት ግዜ እስኪደርስ ድረስ እንቅቦችን ቅርጫቶችን እየሰራ ለዚያ ወዳጅ ለሆነውና ለሚያገለግለው ወንድም ይሰጠውና ያም ሰው እየሸጠ ለዚያች ሃሰተኛ ልጅ እየሰጠ ኖረ::
የምትወልድበት ቀን ሲደርስ እጅግ አስጨነቃት በታላቅ ሲቃይ ውስጥ አራት ቀኖች ያህል ኖረች ለሞትም ተቃረበች እንቱአም ካንቺ የሆነው ምንድን ነው የተሰራ ስራ አለና ንገሪኝ አለቻት እሱአም በ እግዚአብሄር አገልጋይ ላይ ዋሽቻለውና ያመነዘርኩት ከእከሌ ጎልማሳ ጋር ሲሆን በ እውነት ሞት ይገባኛል አለቻት:አባት እና እናቱአም በሰሙ ግዜ ደንግጠው እጅግ አዘኑ የሃገር ሰዎችም ሁሉ ተሰበሰቡ በርሱ ላይ የሰሩትን በደል ይቅር ይላቸው ዘንድ ወደ ቅዱስ መቃርስ ሄደው ለመኑት ያን ግዜ በበረሃ ያየውን ያንን ራዕይ አስታውሶ ይቅር አላቸው ቀድሶም ቅዱስ ስጋውንንና ክቡር ደሙን አቀበላቸው:ክንፉ ስድስት የሆነ ኪሩብ ደግሞ ተገለጠለት ትርጉአመውም የልብ ሚዛን ወደተባለ ወደ አስቀጥስ በረሃ እጁን ይዞ መርቶ አደረሰው:ቅዱስ መቃርስም ያንን ኪሩብ ጌታዬ ሆይ በውስጡ የምኖርበትን ቦታ ወስንልኝ አለው ያ ኪሩብም አልወስንልህም የ እግዚአብሄርንም ትዛዝ አትተላለፍ እነሆ ይህ በረሃ ሁለመናው ላነተ ተሰቱአል እና ወደ ፈለክበት ሄደህ ተቀመጥ ብሎ መለሰለት:ቅዱስ መቃርስም የቅዱሳን ሮማውያን የመክሲሞስና የደማቴዎስ ቦታ ወደ ሆነው ከውስጠኛው በረሃ ገብቶ ኖረ:እነሱም በመጥኡ ግዜ ከርሱ አቅራቢያ ኖረዋልና ከረፍታቸው በሁአላ ግን ሄዶ በዚያ ቦታ እንዲኖር የ እግዚአብሄር መልአክ አዘዘው:ይህውም ዛሬ የሱ ገዳም የሆነው መላእኩ ይህ ገዳም በመክሲሞስ እና በደማቴዎስ በስማቸው ይጠራልሥላለው እስከዚች ቀን ደብረ ብርስም ተብሎ ይጠራል ትርጉአመውም የሮም ገዳም ማለት ነው:የከበረ አባ መቃርስም ታናሽ በአት ሰራ በውስጡአም ሆኖ ያለ ማቁአረጥ በጾም በፀሎት በስግደትም በመትጋት ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ ሰይጣናትም ተገልጠው የሚመጡበትን እና በቀንም በለሊትም በግልጽ የሚዋጉት ሆኑ:በጾም እና በጸሎት ሲጋደል ሰይጣናት እየተዋጉት እርፍትን ስላላገኘ በልቡም እንዲ አሰበ በአለም ውስጥ ሳለው የቅዱስ አባ እንጦንዮስን ዜና ሰምቻለው የምንኩስናን ስራት ያስተምረኝ እና ይመራን ዘንድ ተነስቼ ወደሱ ልሂድ የረከሱ ሰይጣናት የመከሩትን ምክራቸውን እገለብጥ ዘንደ እሱ እውቀትን እና ማስተዋልን ይሰጠኛልና አለ ያን ግዜም ተነስቶ ጸሎት አድርጎ ወደ አረጋዊ አባ እንጦንዮስ ዘንድ እስከሚደርስ ወደ ምስራቅ አቅጣጫ ተጉአዘ አባ እንጦንዮስም ከሩቅ ባየው ግዜ እነሆ ተንኮል ሽንገላ የሌለበት ክርስቲያን አለው በታላቅ ደስታም ተቀብሎ ሳመው:አባት ለልጁ እንደሚገልጥ ሃሳቡን ሁሉ ገለጠለት ይህ አረጋዊ አባ እንጦንዮስም የመቃርስን ራሱን ስሞ ልጄ ሆይ በዮናኒ ቁአንቁአ እንደ ስምህ ትርጉአሜ አንተ ብጹእ ትባላለህ ስራህንና ወደኔ መምጥትህን ፈጣሪ እግዚአብሄር ገልጦልኛል እና ስለዚህ መመጥትህን የምጠባበቅ ህንኩ አለው::
ከዚም በሁአላ ለአባ መቃርስ የከበረች የምንኩስናን ስራት አስተማረው መሰራት በሚገባ በብዙ ነገርም አጸናው ሰይጣናት የሚዋጉት መሆናቸውን እነሱም በስውር በፈቲው ጦር እንዲሁም ጥፋት በሆኑ ስራዎች ሁሉ ይዋጉሃል:አንተ ፍፁም ልትሆን አንተም እስከሞት ደርሰህ ታገስ አሁንም እግዚአብሄር ወደ ወሰነልህ ቦታ ሄደህ ስራህን እየሰራህ በውስጡም ታገስ ብሎ ገለጠለት:ከአባ እንጦንዮስ ዘንድ የምኩስናን ስራት እየተማረ ጥቂት ቀኖች ከኖረ በሁአላ ከተባረከ ኤጲስ ቆጶስ ከአባ ሰራብዮን ጋራ በተማራቸው ህያዋን በሚያደርጉ ትምህርቶች እና ስራቶች ፈጽሞ ደስ እያለው ወደ በአቱ ተመለሰ:
አባ መቃርስም በአባቴ በአባ እንጦንዮስም ዘንድ በነበርኩባቸው ቀኖች ሲተኛ ከቶ አላየውትም አለ:አባ መቃርስም በምንኩስና ስራት ተጠምዶ እየተጋደለ ብዙ ግዜ ኖረ ያ ኪሩብ መላእክም በግልጽ ይጎበኘው ነበር:በአንዲት ቀንም እንዲ የሚለውን ቃል ከሰማይ ሰማ ቃሌን እና ትእዛዘን ሰምተህ ወደዚህ መተህ በዚ ቦታ ውስጥ ስለኖርክ እነሆ ቁጥር የሌላቸውን የብዙ ብዙ ወገኖችን ከነገዶች ከሃገሮች በቁአንቁአ ከተለያዩ ህዝቦች እሰበስባለው እነሱም በዚ ቦታ ያገለግሉኛል የከበረ ስሜንም ያመሰግናሉ በበጎ ስራቸው እና ትሩፋታቸው ደስ ያሰኙኛል አንተም ተቀበላቸው እውነተኛ የድነት መንገድም ምራቸው ይሄንንም ቃል በሰማ ግዜ ተበረታታ ልቡም ፀና በለሊቲም በጸሎት ግዜ ቆሞ ሳለ የክብር ባለቤት ጌታችን ጆሮውን ከፍቶለት ሰይጣናት ሲማከሩ ሰማቸው እንዲህም አሉ ይህን ሰው በዚ በረሃ እንዲኖር ብንተወው የብዙ ብዙ ወገኖችን ይመራቸዋል እንሱም በዚ በረሃ ውስጥ ነዋሪዎች ሆነው የሰማይዋን ሃገር ያደርጉታል እንሱ ለዘላለም ጸንቶ በሚኖር ህይወት ይተማመናሉና እኛንም በሚቀጣ ጸሎታቸው ቀጥተው አሰቃይተው ያሳድዱናልና ከዚ ቦታ ልናሳድደው እስኪ እንችል እንደሆነ ኑ ዛሬ ብሱ ላይ እንሰብሰብ ሲሉ ሰማቸው አባ መቃርስም ይህንን በሰማ ግዜ ልቡ ጸና በሰይጣናት ላይም ተበረታታ የሰይጣናት ምክራቸውን እስከሚሰማ ጆሮውን የከፈተለት እግዚአብሄርን አመሰገን:ደካማነታቸውንም አወቀ ::
ከዚ በሁአላ ይዋጉት ዘንድ ሰይጣናት በርሱ ላይ ተሰበሰቡ በደጁ እሳትን እያነደዱ ከሳቱ እያነሱ ወደ በአቱ ይጨምሩ ጀመር ያቺ እሳት ግን በጸሎቱ የሚጠፋ ሆነች ከዚ በሁአላ እንሣዊ በሆነ ስራ በፍትወት(ዝሙት)ጦር ተውጉት በዚም ታገሰ:ትካዘን አለማዊ ክብር መውደድን ትቢትን መመካትን ታካችነትን ስድብን ሃይማኖት ማጣትን ከእግዚአብሄር ዘንድ ተስፋ መኩረጥን በልቡ አሳደሩበት ከዚ ሁሉ በሚበዛ ተዋጉት የከበረ አባት አባ እንጦንዮስ እንደነገረው በኝህም አጥፊዎች በሆኑ ስራዎች ሰይጣናት እየተዋጉት ረጅም ግዜ ከኖረ በሁአላ ዳግመኛ ወደ አባት እንጦንዮስ ተነስቶ ሄደ ይህም አባት ገና ከሩቅ ሳለ ለደቀ መዛሙርቱ በልቡ ሽንገላ በእውነት የሌለበት ክርስቲያን ነው ልጆቼ ይህን የከበረ ሰው ታዩታላቹን እሱ ለብዙ ወገኖች የቀና የጽድቅ በትር እና ረጅም አላማ ይሆን ዘንድ አለውና:ከአሸናፊ እግዚአብሄር አፍ የተገኘ ጣፋጭ ፍሬም ይሆናልና አለ:ወደ ቅዱስ አባ እንጦንዮስም በቀረበ ግዜ በምድር ላይ ሰገደለት በፍጥነትም ቀና አድርጎ ሳመው ፊቱ እንደበሽተኛ ፊት ተለውጦ አይቶታልና ይህውም ሰይጣናት አብዝተው ስለተዋጉት ነው:ከዚያም ጸሎት አድርገው በአንድነት ተቀመጡ አባት እንጦንዮስ ደስታ በተመላ ቃል ልጄ መቃርስ በደና አለህን? አለው ቅዱስ መቃርስም እነሆ ከኔ የሆነውን ሁሉ እግዚአብሄር ቀድሞ ገልጦልሃል ብሎ መለሰለት:እሱም ያን ግዜ አስተማረው አጽናናው እንዲህም ብሎ መከረው:መንፈሳዊ ጥበብን ለሚሹ ለብዙ ወገኖች መምህራን እንድትሆን ይህቺውም ምንኩስና ናት ከጠላታችን በላያችን የሚመጣብንን መከራ ሁሉ ልንታገስ ለኛ የሚገባ ነው ልጄ መቃርስ ሆይ ውሃ ለመቅዳት ስትሄድ እግዚአብሄር የነገረህን ያንን ቃል አስብ አለው:ቅዱስ መቃርስም ሰምቶ እጅግ አደነቀ የተሰወሩ ስራዎቹ በከበረ አባት ለ እንጦንዮስ የተገለጡለት እንደሆኑ አወቀ በርሱ ዘንድም እየተማረና በረከትን እየተቀበለ ብዙ ቀኖች ኖረ ከዚያም የከበረች አስኬማን ያለብሰው ዘንድ ፈለገ አባ እንጦዮስም በላዩ ጸለየ እርሱአን አስኬማይቱን አለበሰው ስለዚ የከበረ እንጦንዮስ አባት ተባለ::
ዳግመኛም ወደዚህ ወደኔ መመጣትን ቸል አትበል እኔ ከጥቂት ቀኖች በሁላ ወደ እግዚአብሄር ሄዳለውና አለው አባ መቃርስም ይህንን ነገር በሰማ ግዜ ተነስቶ ሰገደለት መንፈሳዊ በረከቱን ይቀበል ዘንድ ከርሱም ዘንድ እንዲኖር ለመነው እሱም ተቀመጥ አለና ተቀመጠ:ዳግመኛም አባ እንጦንዮስ ከጥቂት ቀኖች በሁአላ ሰይጣናት በኔ ላይ እንዳደረጉት በግልጥ ከተዋጉህ በሁአላ ከዚ ከክፉ ሃሳብ ውጊአ እግዚአብሄር ያሳርፍሃል እና በርትተህ ታገስ:እስከ እድሜህ ፍጻሜ ካነተ ጋር ሆኖ እንዲረዳህ እግዚአብሄር ያደረገውን ጠባቂሂን መልአክ እንዳታሳዝነው ተጠበቅ አለው:ከዚ በሁአላ አባ እንጦንዮስ ለአባ መቃርስ በትሩን ሰጠው በመንፈሳዊ ሰላምታ ተሰናብቶት አረፈ:ሲጋውንም ማንም በማያቀው ስውር ቦታ ቀበረው:የከበረ አባ መቃርስም ወደ በአቱ ተመልሶ በአስቀጥስ ገዳም ተቀመጠ ዜናውም በአራቱ መአዘን ተሰማ እግዚአብሄርም በጆቹ አስደናቂዎች ተአምራትን አደረገ::
ከዚህ በሁአላ የከበረ አባ መቃርስ ተመልሶ ከርሱ አስቀድሞ በዚያ አስቄጥስ በርሃ ውስጥ ሰው እንዳለ ያይ ዘንድ ወደ በረሃ ውስጥ ዘልቆ ገባ:ራቁታቸውን የሆኑ ሁለት ሰዎች አይቶ ፈራ የሰይጣን ሚትሃት መስሎታልና 'እልቦት' 'ቦሪቦን' ብሎ በህቡ የ እግዚአብሄር ስም ጸለየ ይህም አቡነ ዘበሰማያት ማለት ነው:እንሱም በስሙ ጠርተው መቃርስ ሆይ አትፍራ አሉት እርሱም በበረሃ የሚኖሩ ቅዱሳን እንደሆኑ አውቆ ወደነሱ ቀርቦ እጅ ነሳቸው እነሱም በአለም ስላሉ ሰዎች ስለ ስራቸው ጠየቁት እርሱም በቸርነቱ እግዚአብሄር በሁሉም ላይ አለ ብሎ መለሰላቸው:እርሱም ደግሞ የክረምት ቅዝቃዘ ይቀዘቅዛቸው እንደሆነ የበጋውን ትኩሳት ያያልባቸው እንደሆነ ጠየቃቸው እነሱም በዚ በረሃ እግዚአብሄር 40 አመት ጠብቆናል የክረምት ቅዝቃዜ ሳይቀዘቅዘን የበጋ ትኩሳት ሳያቃጥለን ኖረናል ብለው መለሱለት:ደግሞ እነደናንተ መሆነ እንዴት እችላለው አላቸው እነሱም ወደ በአትህ ተመልሰህ ስለሃጥያትህ አልቅስ አንተም እንደኛ ትሆናለህ አሉት:ከነሱም በረከትን ተቀብሎ ወደ በአቱ ተመለሰ::
በርሱ ዘንድ መነኮሳት በበዙ ግዜ ጉድጉአድ ቆፍረው መታጠቢያ ሰሩለት ሊታጠብ በወረደ ግዜ ሊገሉት ሰይጣናት ጉድጉአዱን በላዩ ላይ አፈረሱት መነኮሳትም መተው ከጉድጉአዱ አወጡት:እግዚአብሄርም ከዚ አለም መከራ ያሳርፈው በወደደ ግዜ ሁልግዜ የሚጎበኘውን ኪሩብን ወደ እርሱ ላከ እርሱም እኔ ወዳንተ መጥቼ ወስድሃለው እና ተዘጋጅ አለው ከዚያ በሁአላ አባ እንጦንንንና የቅዱሳንን አንድነት መሃበርን ሰማያውያን የሆኑ የመላእክት ሰራዊትን በ እግዚአብሄር እጅ ነፍሱን እስከሰጠ ድረስ ያይ ነበር:መላ የእድሜው ዘመንም 97 ሆነ መጋቢት 27 ቀንም ከዚ ከአላፊው አለም ወደማያልፈው አለም ነፍሱ ሄደች: የቅዱስ መቃርስ ነፍስ ወደ ሰማይ ስታርግ እንዳየ በዚ ነገር ደቀ መዝሙሩ አባ በብኑዳ ምስክር ሆነ:ሰይጣናትን እንደሰማቸው እየተከተሉ መቃርስ ሆይ አሸነፍከን አሸነፍከን እያሉ ሲጮሁ እስካሁን ገና ነኝ አላቸው ወደ ገነት ሲገባ መቃሪ ሆይ አሸነፍከን ብለው በታላቅ ድምጽ ጮሁ የክብር ባለቤት ፈታሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ይመስገን ስሙም ይባረክ ከእጃቹ ያዳነኝ አላቸው:ብሎ መስክሮአል:የስጋውም ፍልሰትም እንደዚ ሆነ እሱ በህይወት ሳለ ስጋውን እንዳይሰውሩ ልጆቹን አዙአቸው ነበር የሃገሩ የሳሱይርም ሰዎች መተው ለደቀ መዝሙሩ ለዮሃንስ ገንዘብ ሰጡ ይንንም ስለገንዘብ ፍቅር ይመክረው እና ይገስጸው የነበረ ገንዘብ ከመውደድ ተጠበቅ የሚለው ነው:እርሱም መርቶ የቅዱስ አባ መቃርስን ስጋ አሳያቸው ወደ ሃገራቸው ሳሱይር ወሰዱ እስከ አረብ መንግስት 160 ዘመን በዚያ ኖረ ደቀ መዝሙሩ ዮሃነስ ግን ገንዘብ ስለመውደዱ ዝልጉስ ሆነ::
ከዚያም በሁአል ልጆቹ መነኮሳት ወደ ሃገሩ ወደ ሳሱይር ሄዱ የከበረ አባት የአባ መቃርስን ስጋ ሊወስዱ ፈለጉ:የሃገሩ ሰዎችም ከመኮንኑ ጋር ተነስተው ከለከሉአቸው በዚያችም ለሊት የከበረ አባ መቃርስ ለመኮንኑ ተገልጦ ተወኝ ከሊጆቸ ጋር ልሂድ አለው መኮንኑም መነኮሳቱን ጠርቶ የአባታቸውን ስጋ ተሸክመው ይወስዱ ዘንድ ፈቀደላቸው:በዚአን ግዜም ተሸክመው አክብረው ወሰዱት በብዙ ምስጋና በመዘመርም እግዚአብሄርን እያመሰገኑ ነሃሴ 19 ቀን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አኖሩት ከሱም ታላላቅ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ::
ለእግዚአብሄር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ አባ መቃርስ እና በአባ እንጦንዮስ ፀሎት እና አማላጅነት የምትገኝ በረከት ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች እንዲሁም ከሃገራችን ከኢትዮጵያ ጋር ለዘላለም ይኑር አሜን!!!!!!...................ቸር ያቆየን.

No comments:

Post a Comment