Monday, August 9, 2010

ውዳሴ ማርያም አንድምታ የሰኞ ክፍል 1

ይኸነን መጽሐፍ ኤፍሬም ሶርያዊ ኤፍሬም ለብሐዊ ተናግሮታል፡፡ ሶርያዊ በሀገሩ ለብሐዊ በተግባ ያስኛል፡፡ ይህም ቅዱስ ኤፍሬም የያዕቆብ ዘንጽቢን ደቀ መዝሙር ነው፡፡ ያዕቆብ ዘንጽቢንም ቁጥሩ ከሰለስቱ ምዕት ነው፣ ለአውግዞተ አውአርዮስ ሲሄድ አስከትሎ ሂዶ ነበር፡፡ አርዮስ አውግዘው ሀይማኖት መልሰው ተመልሰው ካደሩበት ቦታ አምደ ብርሃን ከምድር እስከ ሰማይ ተተክሎ ለሊቱን በህልሙ ራዕይ ያያል፡፡ ራዕዩም እንደገለጽክልኝ ባለበኔቱንም ግለፅልኝ ብሎ ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክት የታዘዘ መልአክ መጥቶ ባስልዮስ ዘቂሣርያ ነው፡፡ለቤተ ክርስቲያን አምድ ፅንዕ ነውና በትምህርቱ የሰውን ልቦና ብሩህ ያደርጋልና እንዲህ ባለ አርአያ አየኸው አለው፡፡ ባስልዮስም ቁጥሩ ከሰለስቱ ምእት ነው ደረሶም ተመልሶም እንደ ሆነ በደዌም በዕርግናም ምክንያት ቀርቶ እንደሆነ የቀረበት ምክንያት ከዚህ በኃላ መምህርን ካወጡበት ሳያገቡ ትቶ መሄድ ፈሊጥ አይደለምና መምህን ካወጣበት አግብቶ ሰለሦስተ ነገር ይሄዳል መጀመሪያ እንዲህ ካለ ሰው ጋራ ቢጫወቱ መንፈሳዊ ነገር ይገኛልና ብሎ ሁለተኛ በጆሮ የሰሙትን በዐይን ቢያዩት ይረዳልና ብሎ ሦስተኛ የመንፈስ ቅዱስን ነውን ወይስ ሰይጣን ተጫውቶብኝ ይሆን ብሎ ስለ ሄደ ግን እንዳየው ሆኖ አላገኘውም በወርቅ ወንበር ተቀምጦ በወርቅ አትራኖስ የወርቅ ወንጌል አቀርግቶ ካባ ላንቃ ለብሶ ኪፋር ጠምጥሞ መነነሳንሱን ቢያዩት የሐር መያዣውን በያዩት የወርቅ መነሳንስ ይዞ ሲያስተምር አግኝታል፡፡ ወተሐዘቦ ልቡ ለኤፍሬም ከመ ሥጋዊ ውእቱ እንዲል፡፡
እስመ ሚስጥራትን ይትከሠታ ለትሑታ እስመ ውስተ ምይንት ነፍስ ኢተኀድር ጥበብ አንዲል፡፡ ወይሬእዩ ርእሶሙ ከመ መነፈስ እንተ ህልፈት ይላል ለመንፈስ ቅዱ ሁለት ግብ አለውን ወይስ ሰይጣን ተጫውቶብኝ ይሆን እያለ ሲያወጣ ሲያወርድ ዐራት ነገር አይቶ ይረዳል፡፡ መጀመሪያ ካፋ ነጸብራቅ እሳት እየወጣ ሕዝቡንም ሲዋሃዳቸው ያያል ይህም ትምህርቱ ነው፡፡ ሁለተኛ እርብ መጥታ በራሱ ላይ ስታርፍበት ሦስተኛ ተሐዋስያን ከልብሱ ላይ እያረፋ እንደቆሎ ሲረግፍ ያያል፡፡ ይህን መናፍቃን ፍጡር ፈጣሪ ይመስላ ያቃጥላልን ብለው እንቃወማለን ይላሉ አይፈርስም ለከዊነ እሳት ደርሶ ነበርና ያቃጥላል ዐራተኛ ስሙን ያያውቅ ሀገሩን ያይጠይቅ ኤፍሬም ሶርያዊ ኤፍሬም ለብሐዊ ብላችሁ ጥሩልኝ ከማእዘነ ቤተ ክርስቲያን ባንዱ ቆሞ ይጸልይላችኋል ብሎ አስጠርቶ በአስተርጓሚ ሲጫወቱ ጨዋታው ባይከተትለት አባቴ ጸልይና ያንተ ቋንቋ ለእኔ ይገለጥልኝ፡፡

ጸልዮ የባስልዮስ ቋንቋ ቅርዕ ነው ለኤፍሬም የኤፍሬም ቋንቋ ሱርስት ነው ለባስልዮስ ለገልጾላቸው ሲጨዋወቱ አድረው ሲነጋ አሰናብተኝ ሊሂድ አለው፡፡ መች ልትሄድ አምጥሃላ ልትኖር ነው እንጂ ብሎ ሕዝባዊ ነው ቢሉ ዲቁና ዲያቆን ነው ቢሉ ቅስና ሽሞ ከሀገረ ስብከቱ ሀገር ከፍሎ አስተምር ብሎ ሰጠው፡፡ በሰልዮስም ይህን መልበሱ ስለ ክብረ ወንጌል ነው፤ ዛሬ ካህናት አክሊል ደፍተው ኩፋር ጠምጥመው ካባ ላንቃ ለብሰው ስጋውን ደሙን እንዲያከብሩ እንዲለውጡ እርሱስ በውስጥ የሚለብሰው ማቅ ነበር፡፡ ከዚህ በኃላ እም አዝማደ ነገስታት ይላታል ከአዋልደ ነገስታት ወገን የምትሆን አንዲት ሴት ነበረች ኃጢያቷን እየፃፈች የምታኖር፡፡ ስለምን ቢሉ ለመንገር ብታፍር፡፡ አንድም ቢበዛ፡፡ አንድ ቀን መጥታ እንደተጠቀለለ ይዛ አባቴ በዚህ ያለው ይፋቅልሽ በለኝ አለችው፡፡ ይፋቅልሽ አላት ገልጣ ብታይ አንዲት ቀርታ አየች ዘዕጽብ ለነጊር ለገቢርም ይላታል ይህችሳ አለችው ይህስ ለቅዱስ ኤፍሬም ቢቻል እንጂ ለእኔ አይቻለኝም አላት፡፡ አሁን ለእርሱ የማቻለው ሆኖ አደለም ቅዱሳን የራሳቸው ክብር ኪገለጥ የወንድማቸው ክብር ቢገለጥ ይወዳሉና፡፡ ዳግመኛም ስጥመጣ ስትሄድ ድካም ያለባት ነውና ቀኖና ይሁናት ብሎ ነው ሄዳ አባቴ በዚህ ያለው ኃጥያትሽ ይፋቅልሽ በለኝ አለችው

ይህስ ለሊቀ ጳጳሱ ለቅዱስ ባሰልዮስ ቢቻለው እንጂ ለእኔ አይቻለኝም አላት አሁን በእርሱ የማይቻለው ሆኖ አይደለም፡፡ ቅዱሳን የራሳቸው ክብር ኪገለጥ የወንደማቸው ክብር ቢገለጥ ይወዳሉና፡፡ ዳግመኛም ስትሔድ ስትመጣ ድካም ያለባት ነውና ቀኖና ይሁናት ብሎ፡፡ ስለሄድሽ ግን እንደቀደመው በህይወተ ስጋ አታገኝውም ሙቶ ሊቀብሩት ይዘውት ሲሄዱ ታገኝያለሽ ሳትጠራጠሪ ከአስክሬኑ ላይ ጣይው ይፋቅልሻል፡፡ ብትሄድ ሙቶ ሊቀብሩት የዘውት ሲሄዱ አገኘች አትጠራጠር ካስከሬኑ ላይ ብትጥለው ተፍቆላታል ይህም የካህናትን ማዕርግ ደግነት ይጠይቃል፡፡ በህይወተ ስጋ ሳሉ ከሞቱም በኃላ አጢያት እንዲያስተሰርዮ ስምኦን ዘአምድ የያዕቆብ ዘንጽቢን ደቀ መዝሙር ነው አብሮት ተምሯል ሊጠይቀው መጣ ሰላም ለኪ ኦ እግዝእትየ ቅድስት ድንግል እያለ ሲያስተምር ሰማሁ፡፡ ኦ እግዝእትየ ከማን አገኘኸው መምህራችን አልነገረን አለው፡፡ ነግሮናል እንጂ አልነገረንም ይመስክር ተባብለው ከመቃብሩ ላይ ቢሄዱ አስሩ ጣቶቹ እንደ ፋና እያበሩ ተነስቶ በህይወትየ እብለኪ ሰላም ለኪ ኦ ቅድስት ድንግል ከመ ስምኦን ዘአምድ፡፡ ወድህረ ሞት የሰ ኩሎሙ አዕፅምትየ ይብሉኪ ወይወድሱኪ ሰላም ለኪ ኦ እግዝእትየ ድንግል ከመ ኤፍሬም ሶርያዊ ብሎ መስክሮለታል፡፡

ይህም የቅዱስ ኤፍሬም ጸጋው ክብሩ ነው፡፡ ከሞተ በኋላ የሚናገረውን አውቆ ለማመስገን ሶርያዊ በሀገሩ ያሰኘው እስከዚህ ነው፡፡ ለብሐዊ በተግባሩ ቢረሌ በርጠብ ብርጭዎ ኩዝ ካቦ እየሰራ የዐመት ልብሱን የዕለት ምግቡን እያስቀረ ይመፀውት ነበር ሲመፀውትም መስላሴ በመላእክት በፃድቃን በሰማዕታት ስም አይመፀውትም በእመቤታችን ስም ይመፀውት ነበር ንቋቸውን አጥቅቷቸውን ነውን ሰለምነው ቢሎ ንቋቸም አጥቅ ቷቸውም አይደለም የእመቤታችን ፍቅር ባያደርሰው ነው፡፡ እመቤታችንን ከመውደዱ የተነሳ የእመቤቴ ምስጋናዋ እንደሰማይ ኮከብ እንደ ባህር አሸዋ በዝቶልኝ እንደልብስ ለብሼው እንደ ምግብ ተመግቤው ጠግቤው እያለ ሲመኝ ይኖር ነበር፡፡ የሹትን መግለጽ እግዚአብሔር ልማዱ ነውና፡፡ ገልጾለት ፼ ካ4 ሺህ ድርሰት ደርሷል አኃዝ እግዚኦ መዋግደ ጸጋከ እስኪል ድረስ፡፡ የሚጸልየውም ጸሎት ከሉቃስ ወንጌል ወበሳድስን ጸሎተ እግዝእትነ ማርያምን አውጥቶ ፷4 ፷4 ጊዜ ይጸልይ ነበር፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ዕለቱ ሰኑይ ጊዜው ነግህ ነው፡፡ የነግህ ተግባሩን አድርሶ ከመካነ ግብሩ ተቀምጦ ሳለ እመቤታችን ትመጣለች የብርሃን ምንጣፍ ይነጠፋል የብርሃን ይዘረጋል ከዚያ ላይ ሁና ሰላም ለከ ኦ ፍቁርየ ኤፍሬም ትለዋለች፡፡ እሱም ታጥቆ እጅ ነስቶ ይቆማል፡፡ ወድሰኒ ትለዋለች እፎ እክል ወድሶተኪ ዘኢይክሉ ሰማያውያን ወምድራውያን፡፡ ምድራውያን ጻድቃን ሰማእታት ሰማያውያን መላእክት አንቺን ለማመስገን የማይቻላቸው ለእኔ እንደምን ይቻለኛል አላት፡፡ በከመ አለበወከ መንፈስ ቅዱስ ተናገር አለችው፡፡ በተረቱበት መርታት ልማድ ነውና፡፡ እፎኑ ይከውነኒ ዝንቱ እንዘ እየአምር ብእሴ ብትለው፡፡ መልአኩ መንፈሰ እግዚአብሔር ቅዱስ ይመጽ ላእለኪ ብሏት ነበርና፡፡ ከዚህ በኋላ በርክኒ ይላታል፡፡ በረከተ ወልድየ ወአብሁ መንፈስ ቅዱስ ይኀድር በላእሌከ ትለዋለች፡፡ ተባርኮ ምስጋናዋን ይጀምራል፡፡ ሲያመሰግናትም ደቀ መዝሙር ቅኔ ቆጥሮ እንዲቀኝ ድርሰት አስቦ እንዲጽፍ አይደለም፡፡ ብልህ ደቀ መዝሙር ያጠናውን ቀለም ከመምህሩ ፊት ሰተት አድርጎ እንዲያደርስ እንደዚያ ነው፡፡ ስታደርሰውም ከሰባት ከፍላ አስደርዋለች፡፡ ስለምን ቢሉ በሰባቱ ዕለታት መመስገን ፈቃድዋ ቢሆን፡፡ አንድም ሰባቱ ዕለታት ምሳሌዋ ናቸውና በዕለቱ እሁድ ትመሰላለች፡፡ በዕለተ እሁድ አስራወ ፍጥረታት አራቱ በህርያት ተገኝተዋል፡፡ ከሷም ለዘኮነ ምክንያተ ፍጥረት በፍላዌሁ እንዲለው አስራወ ፍጥረት ጌታ ተገኝቷልና፡፡ በዕለተ ሰኑይ ትመሰላለች፡፡ በዕለተ ሰኑይ ከዚህ እስከ ብሩህ ሰማይ መልቶ የነበረውን ውሃ ከሶስት ከፍሎታል፡፡ አንዱን እጅ ከላይ ሰቅሎታል ሐኖስ ነው፡፡ አንዱን እጅ በዙርያው ወስኖታል፡፡ አንዱን እጅ አጽንቶ የብርሀን ማህደር አድርጎታል ጠፈር ነው ጠፈር የእመቤታችን ብርሃን የጌታ ምሳሌ፡፡ ይህማ የጠፈር ምሳሌ ሆነች እንጂ መቼ የዕለቲቱ ምሳሌ ሆነቻ ብሎ የዕለቲቱን የእሷ ጠፈር የእርሷ የተነሳው ስጋ ብርሃን የጌታ ምሳሌ፡፡ በዕለተ ሰሉስ ትመስላለች፡፡

በዕተ ሰሉስ ለታብቁል ምድር ሀመልማለ ሳእር ዘይዘራዕ በዘርዑ ወበበ ዘመዱ በበ አርአያሁ ወበበ አምሰሊሁ ባለ ጊዜ በእጁ የሚለቀሙ አትክልት በማጭድ የሚታጨዱ አዝእርት በምሳር የሚቆረጡ እፀዋት ለስጋውያን ምግብ የሚሆኑ ተገኝተዋል ከእሷም የመንፈሳዊያን ምግብ የሚሆን ጌታ ተገኝቷልና፡፡ በዕለተ ረቡዕ ትመሰላለች በዕለተ ረቡዕ ለይቁሙ ብርሃናት በቀጸ ሰማይ ባለ ጊዜ ለስጋው ያን ምግብ ጠየሚሆኑ ፀሃይ ጨረቃ ከዋክብት ተገኝተዋል፡፡ ከእሷም ለመንፈሳዊያን ምግብ የሚሆን ጌታ ተገኝቷልና፡፡ በዕለተ ሐሙስ ትመሰላለች በዕለተ ሐሙስ ለታወጽእ ባህር ዘቦ መንፈሰ ህይወት ባለ ጊዜ በልባቸው የሚሳቡ በእግቸው የሚሽከረከሩ በክንፋቸው የሚበሩ የደመ ነፍስ ህያዋን ሁነው የሚኖሩ ፍጥረታት ተገኝተዋል፡፡ በረው በረው የሄዱ አሉ ከዚም የቀሩ አሉ፡፡ በረው በረው የሄዱት የኢጥሙቃን ከዚያው የቀረት የጥሙቃን ምሳሌ፡፡ ያስወባርኮሙ ለክልኤሆሙ በአሃቲ በረከት ይላል ብሎ ብላባቸው የሚሳቡ የሰብአ ዓለም በእግራቸው የሚሳብ ከትሩፋት በደትሩፋት የሚሄዱ ባህታውያን በክንፋቸው የሚበሩ ተመስጦ ያላቸው የሰማዕታት ምሳሌ፡፡ ዕለቲቱ የሱዋ ባህር የጥምቀት ምሳሌ፡፡ በዕለተ አርብ ትመሰላለች በዕለተ አርብ በኩረ ፍጥረት አዳም ተገኝቷል፡፡ ዳግማዊ አዳም ጌታም ከእሳ ተገኝቷልና፡፡ በዕለተ ቀዳሚት ትመሰላለች፡፡ በዕለተ ቀዳሚት ስጋዊ እረፍት ተገኝቷል፡፡ ወእረፈ እግዚእነ እምኩሉ ዘአኃዘ ይግበር እንዲል ከሷም የመንፈሳውያን እረፍት ጌታ ተገኝቷልና ውዳሴ ዘሰኑይ ውዳሴ በአኑይ ውዳሴሃ ለእግዝእትነ መርያም ዘይትነበብ በዕለተ ሰኑይ ቡል በአንድ ነው ቃለ ጸሃፊ ነው፡፡ እሱ ግን ምስጋናዋን ፈቀደ እግዚእ ብሎ ይጀምራል፡፡ በእለተ ሰኑይ የሚነበብ የሚጸለይ የሚተረጎም አምላክን የወለደች የእመቤታችን ምስጋናዋ ይህ ነው ::
‹‹ፈቀደ እግዚእ ያግዕዞ ለአዳም ኁዙነ ወትኩዘ ልብ፡፡››
እምስት ሺህ ከ5፻ ዘመን በግብርና ዲያብሎስ የነበረ አዳምን ነጻ ያደርገው ዘንድ ወደደ፡፡ ህዙነ ልብ ትኩዘ ልብ ሲል ነው፡፡ ተምያጠ ወተውላጠ ህላዌያት ጽጌያት ወፍያት ትሩፋት ስመ ወግብረ ወልድ እንዲል፡፡ ወክብረ ወልድም ይላል፡፡ አንድም ያዘነ የተከዘ ሊያድነው ወደደ አዳምን የቤተ ፊት ልማድ አላገኘውም፡፡ ቤተ ፈት በዚህ ጊዜ እበላ እጠጣ ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ተድላ ደስታ አደርግ ነበር እያለ ያእናል እርሱ ግን አትብላ ያለኝን እጸ በለስ በልቼ ከፈጣሪዬ ትእዛዝ ወጣሁ ብሉ ነውና፡፡ በአልቦቱ ካልእ ኅሊና ዘንበለ ብካይ ላዕለ ኃጢያቱ እንዲል አንድም ጌታ ያዘነ የተከዘ ሆኖ አዳምን ነጻ ሊያወጣው ወደደ፡፡ ተከዘት ነፍስየ እስከ ለሞት እንዲል አመስግነኝ ብትለው ምነው ወደ ሌላ ሄደ ቢሉ፡፡ ወደ ሌላ መለሄዱም አይደል አዳምን አስከትላው መጥታ ነበር እና ቢያየው አነሳው፡፡ አንድም ነገር ከስሩ ውሃ ከጥሩ እንዲሉ አዳም አባቷ ነውና፡፡ ከጥንት ጀምሮ ተርኮ ለመናገር ይሏል፡፡ ያስ ቢሆን ስለመን ፈቀደ እግዚእ አለ ቢሉ መክበሪያዋን ሲሻ ከዚያ ሁሉ ታኦፊላ ሊቃስን ዜና ሐዋርያትን ፅፈሕ ስደድልኝ ቢለው እም ጊዜ እርገሩ ለእግዚእነ እናዳለ መክበሪያቸው ሲሻ፡፡
‹‹ወያግብኦ ኀበ ዘትካት መንበሩ፡፡››
ወደ ቀደመ ቦታው ወደ ቀደመ ክብሩ ይመልሰው ዘንድ ወደደ ክብር ቢሊህ ልዩነት ቦታ ቡሉ ገነት ፍጡር ከሆነ ያለ ቦታ መኖር አይቻለውምና ከዚያውም ዘንድ ካለመደው የለመደውን ቢሰጡት ደስ ይለዋልና ይህማ ለሰማይና ለምድር ምን ቦታ አላቸው ቦታቸው እርሱ አይደለምን አሀዜ ዓለም በእራሁ ኩሉ እሁዝ ውስጥ እዴሁ ይጸውር ድደ ወነብር ጠፈር እንዲል ለሰማይና ለምድር ምን ቦታ አላቸው ቦታቸው እሱ አይደለምን ቢሉ የዕርቅ ምልክት ነው ንጉስ የተጣላውን የሳናፊልህን አትታጠቅ እንዲህ ካለ ቦታ አትውጣ ብሎ ወስኖ ያግዘዋል በታረቀው ጊዜ ርስቱን ጉልበቱን ቤቱን ንብረቱን ይመልስለታል እንደዚህም ሁሉ የዕርቅ ምልክት ነው፡፡
‹‹ሰአሊ ለነ ቅድስት፡፡››
5 ሺሕ ከ5፻ ዘመን በግብርናተ ዲያብሎስ የነበረ አዳምን ነፃ ካደረገው ልጅሽ እመቤታችን ንጽህት በድንግልና ጸጋው ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን ቅድስት አለ ንጽህት ጽንዕት ክብርት ልዩ ሲል ነው ንጽህትም አለ ሌሎች ሴቶ ከነቢብ ከቢር ቢነጹ ከኃሊዮ ዓየነጹም ርሷም ነቡብ ከገቢር ከሀልዮ ንጽህት ናትና፡፡ ወኢርኩሰት በምንትኒ እንዘፈጠራ ድንግል በህልናሃ ወድንግል በሥጋሃ አንዲል፡፡ ጽንዕትም አለ ሌሎች ሴቶች ቢጸኒ ለጊዜው ነው ኋላ ግን ተፈትሆ አለባቸው፡፡ እርሷ ግን ቅድመ ጸኒስ ቅድመ ወሊድ፤ ጊዜ ወሊድ ድህረ ወሊድ ጽንዕት ናትና ክብርትም አለ ሌሎችን ሴቶች ብናከብቸው ጻድቃንን ሰማዕታትን ወለዱ ብለን ነው እርሷ ግን ወላዲተ አምላክ ብለን ነውና ልዩም አለ እናትነትን ከድንግልና አስተባብራ የምትገኝ ከእመቤታችን በቀር ሌላ ሴት የለችምና፡፡ ዓይኑ ዐ ቢሆን አእመንሮው ለብዎውን ሳይብን አሳድሪብን፡፡ አላፋው አ ቢሆን ለምኚልን ማለት ነው፡፡ ልመናስ ከዚያ በኋላ እንኳን በእሷ ሌሎችን የለባቸውም በቀደመ ልመናዋ የምታስምር ስለሆነ እንዲህ አለ እንጂ ሰአሊ ለነ ቅድስት፡፡ ማን ተናግሮታል ቢሉ ኤፍሬም ተናግሮታል ይኽማ እንዳይሆን በግብጻውያን መጽሐፋቸውን በቃላቸው አይገኝምእሳ ብሎ ቅዱስ ያሬድ ለዜማ መክፈያ ተናግሮታል አንድም የኋላ ሊቃውንት ተናግረውታል
‹‹ሰረቀ በስጋ እምድንግል ዘእንበለ ዘርአ ብእሲ ወአድሀነነ፡፡››
ብረሃን ብሎ የሚመጣ ነውና እንደ አርእስት ሰረቅ ብሎ አነሳ ፈቀደ ብሎ ነበርና ወዶም አልቀረብ ዘር ምክንያት ሳይሆነው ከድንገል በስጋ ተወለደ፡፡ ተወልዶም አዳነን፡፡ በስጋ አለ በመለኮቱ አትወልደውምና፡፡ አኮ ወልደ ማርያም በመለኮቱ አላ በከመ ስርዓተ ትስብእቱ እንዲል፡፡ ልደቱ ለዘርያላደረገው እንደበለ ዘርእ ያደረገው ስለምን ነው ቢሉ ቀዳማዊ ልደሩን ለመግለጽ 5ሺህ ከ5፻ ዘመን ኢፈጸም ከእመቤታችን ያለ አባት መወለዱ ቅድመ ዓለም አብ ያለ እናት እንደ ተወለደ ይጠየቃልና፡፡ ልደት ቀዳማዊ ተዓውቀ ወደኃራዊ እንዲል፡፡ ዳግመኛም በዘርዕ በሩካቤ ተዋልዶ ቢሆን እርቅ ቢእሲ ባሉት ነበርና፡፡ ሶበሰ ተወለደ በሩካቤ ብእሲ ውቢእሲት ዘከማየ ብዙኃን እምተሃዘብዎ ወዕምረ ሰይዎ ሀሰት እንዲል፡፡ ያውስ ቢሆን ተፈትሆ ካላት ያላደረገው ተከሌላት ያደረገው ስለምን ነው በሉ ትንቢቱ መሳሌው ሊፈጸም፡፡ ተንቢት ናሁ ደንግል ትጸንስ ልትወልድ ወልደ ተብሎ ተነግሯል ምሳሌው አዳም ከህቱም ምድር ተገኝቷል፡፡ ጌም በህቱም ማኅጸን ለመወለዱ ምሣሌ፡፡ ሄዋን በህቱም ገቦ ተገኝታለች ጌታም በህቱም ማኅጸን ለመወለዱ ምሣሌ፡፡ ቤዛ ይስሃቅ በግዕ ከእህቱ ጉንድ ተገኝቷል ቤዛ አለም ክርስቶስን በእህቱ ማህጸን ለመወለዱ ምሳሌ፡፡ ጽምዐ እስራኤልን ያበረደ ውሃ ከህቱም እብን ተገኝቷል ጽምዐ ነፍሳትን ያበረደ ማየ ሕይወት ጌታን በህቱም ማህጸን ለመገኘቱ ምሣሌ ጽምዐ ሶምሶንን ያበረደ ውሃ በህቱም መንሰከ አድግ ተኝቷል ጽንዐ ኃጢያትን ያበረደ ማየ ሕይወት ጌታን በህቱም ማህጸን ለመገኘቱ ምሳሌ ትንቢቱን አውቆ አናግሯል ምሳሌውንም አንዲህ አውቆ አስመስሏል ፍጻሜው እንደምነው ቢሉ ከመ ትኩን መራሀተ ለሀይማኖት አባይ አንጂ ይላታል ብትወለደው ማህተመ ደንግልናዋ እንዳለተለወጠ ሰው ሲሆን አምላክነቱ ላለመለመጡ ድንግል ወሰብእ ሲባል ለመኖሩ ምሣሌ ነውና፡፡ ‹‹ሌሄዋ አንተ አስኃታ ከይሲ›› ከይሲ ባሳታት በሄዋን ምነው ከይሲ አለ ዲያብሎስ አይደለም ያሳታት ቢሉ በልሳኑ ከይሲ ተሰውሮ ነውና አንደም በማህደሩ ከይሲ አለው ህዳሪ በማህደር ማህደርን በህዳሪ መጥራት ልምድ ነውና አንድም በግብሩ ከይሲ አለው እባብ በመርዙ እንዲጎዳ ዲያብሎም በግብሩ በነገሩ ይጎዳልና፡፡
‹‹ፍትሀ ላእሊሀ እግዚአብሔር እንዘ ይብል ብዙህ አብዝኖ ለህማምኪ ወለጸአርኪ፡፡››
ጻርሽን ጋርሽን ምጥሽን አበዛዋለሁ ብሎ ከፈረደባት በኋላ በህማም ለዲ ወለድኪ ይኩን ምግባ እኪ ህበ ምትኪ አንዲል፡፡
‹‹ዘምረ ልቡ ኅበ ፍቅረ ስብእ ወአግአዛ፡፡››
ሰውን ወደደና ዋዌውን ታግሶ (አግአዛ) ነጻ አደረጋት ፍቅር አሀቦ ለወልድ ኃያል እመንበሩ በአብጸሆ እስከ ለሞት እንዲል ሄዋን ምክንያተ ስህተት ናት ከሲኦል አልወጣችም የሚሉ መናፍቃን ነበሩና በገአዛ አላባቸው አንድም አስከትላት መጥታ ነበርና ቢያያት አነሳት፡፡
‹‹ሰአሊ ለነ ቅድስት፡፡››
ሄዋንን ነጻ ካደረ ልጅስ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጻጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኚልን እየሱስ ክርስቶስ ቃል ዘተሰብዐ ፈቃደ ሰምረ ያልኩት ሰው የሆ ነው እየሱስ ክርስቶስ ነው ይህም ስም ብቻ የመለኮት ብቻ የትስብ እናት ስም አይደለም ከሁለት አካል አንድ አካል ሁለት ባህርይ አንድ ባህርይ ቢሆን ከሁለት ባህርይ በሆን የወጣት ስም ነው እንጂ፡፡ ወእነግር አነሂ ከመ ይመፍትው እስምዮ በቃለ እግዚአብሔር ክርስቶስ ዘእምበለት ትስእብት ወኢ ለትስብእት ዘንበለ መለኮት ክርስቶስ የሰመይ ወእም ቅድመ ትስጉት አልቦ አይሰምዮ በዝንቱ ስም ልቃለ እግዚአብሐየር ክርስቶስ አንዲል፡፡
‹‹ ማህደረ ላእሌነ ፡፡››
ተሰብአና ኃደረ እንደ አለቀና እንደ ጠበቃ ይጠባበቃሉ ኃደረ ያለውን ይዘው ኀድረት እንዳይሉበት ተሰበአ አለባቸው፡፡ ተሰብአ የለውንም ይዘው ተለወጠ እንዳይሉበት አልነሣም ምትሐት ሥጋ በቅድምና ነበረ ባሕርዮን አግዝፎ ታየ የሚሉ መናፍቃን አሉና ላዕሌነ አለባቸው፡፡ ወውስቴትነ ይላል በጽርዕ ምላሹ፡፡ እንደ መስኖ ውሃ ገብቶ ወጣ የሚሉ መናፍቃን አሉና ስጋንም ነፍስንም እንደተዋሃደ ለመጠየቅ ላእሌነ ወውስቴትነ አለባቸው፡፡
‹‹ ወርኢነ ስብሀቲሁ ከመ ስብሀተ አሐድ ዋህድ ለአብሁ፡፡››
ለአባቱ እንደ አንድ ልጅ የሚሆን ክብሩን አየንለት፡፡ ለአባቱ አንድ ልጅ የሆነ ደጅ አፍ የመሰለው ማጀት የጎረስው ሁሉ ገንዘቡ ነው ለእርሱም የአብ ገንዘብ ሁሉ ገንዘቡ ነውና እስመ ኩሉ ዘቦ ለአቡየ ዚአየ ውእቱ እንዲል፡፡ አንድም ለአባቱ እንደ አንድ ልጅነቱ የሚሆን ክብሩን አየንለት ወይሰገድ ከመ ዋህድ እንዲል አንድም ያባቱን ጌትነት በደብረ ሲና እንዳየ የእርሱንም ጌትነት በደብረ ታቦር አየንለት አንድም አባቴ ኤልያስ አድሮ አንድ ምውት ኤልሳእ አንድሮ ሁለት ምውት ሲያስነሳ እንዳየነው፡፡
እሱም ስጋን ተዋህዶ የአራት ቀን ሬሳ አልአዛርን ሲያስነሳ አየነው የብሉይንም ለአብ የሐዲሱን ለወልድ ሰጥቶ አድሎ መናገር ልማድ ነው እንጂ፡፡ ሁሉም በሁሉ አሉ ያውስ ቢሆብ ወዴት ነበርና ርኢነ አለ ቢሉ የብረሉይን የእነሙሴን ዓይን አድርጎ፡፡ የሃዲሱን የእነጴጥሮስ ዓይን አደርጎ ከዚያ ሁሉ አባ ህርያቆስ ንህነ እሙንቱ እለ በላዕነ ምስሌሁ እምድኀረ ትንሣኤሁ አንዳለ፡፡ የሓዋርያትን መብል መብል አደርጎ፡፡
‹‹ ሠምራ ይሣዐለን፡፡››
ይቅር ይለን ዘንድ ወደደ ሦስት ጊዜ ፈቀደ ሠምረ እለ ለአዳም ለሔዋን ለሕፃናቱ፡፡ ለሥጋ ለነፍስ ለደመ ነፍስ እንደ ካሰ ለማጠየቅ
‹‹ ሰአሊ ለነ ቅድስት፡፡››
ይቅር ይለን ዘንድ ከወደደ ለ3ጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን አንዳነሣን ለምኚልን፡፡
‹‹ርእየ ኢሳይያስ ነቢይ በመንፈስ ትንቢት የምስጢር ለዓመኑኤል፡፡››
ነቢዮ ኢሳያስ ትንቢት በሚገልጽ በመንፈስ ቅዱስ የዐደማኑኤልን ምሥጢር አየ አጸና፡፡
‹‹ ወበእንተዝ ጸርሐ አንዘ ይብል፡፡›› ስዚህ ነገር አሰምቶ ተናገረ፡፡ ዐማኑኤል መለት ሰው የሆነ አምላክ ማለት ነው አዝ ስም ዐቢይ ጥቀ ወአይደሉ ፈሊጦቶ አንዲል፡፡ ጸርሐ አለ ጮሆ የተናገሩት ከሩቅ እንዲሰማ ነገሩ ጽንፍ እሰከ ጽንፍ ይደርሰልና፡፡ ጸርሐ አለ አንጂ ተናገረ ሲል ነው፡፡
‹‹ ሐፃን ተወልደ ለነ፡፡››
ሕፃን ተወለደልን፡፡
‹‹ውልድ ተውሃበ ለነ፡፡››
ወልድ ለሕማም ለሞት ተሰጠልን አንድም ወልድ ተውሀበ ለነ ለኩነተ ሥጋ ተሰጠልን ወሕፃን ተወልደ ለነ ሕጻንም ሆኖ ተወለደልን፡፡ ለመለኮት የአካልም የክብርም ሕፀፅ ነበረበት ሥጋ ምላት ሆነው የሚሉ መናፍቃን ነበሩና ለነ አለባቸው ለርሱ ቢሆን ሎቱ ይል ነበር፡፡ ይህም ደበአርዮስ ያሳይበታል፡፡
‹‹ ሰአሊ ለነ ቅድስት፡››
ወልድ ዘበላዕሉ ሕጸን ዘበታህቱ ከሚባል ልጅሽ እመቤታችን ጽንዕጽ በድንግልና ጸጋውን ክብሩን አንዲያሣ ለምኚልን፡፡
‹‹ ተፈሣሕ ወተሐሠይ ኦ ዘመደ ዕጓለ እመሕያው፡፡››
ባሕርየ ዕጓለ እመሕያው በውሰጥ በአፍአ በነፍስሰ በሥጋ ደስ የበልህ፡፡
እሰመ አፍቀሮ እግዚብሔር ለዓለም፡፡
እግዚአብሔር ሰውን ወዶታልና፡፡
‹‹ ወመጠወ ወልዶ ዋህደ፡፡››
ልጁን ለሕማም ለሞት እስከ መስጠት ደርሶ፡፡ አንድም ወዶ ምን አደረገለት፡፡ ትለኝ እንደሆነ ተቀዳሙ ተከታይ የሌለው ልጁን ለሕማም ለሞት አሳልፎ እግዚአብሔር ለዓም፡፡ እስከ ወልዶ ዋሕደ መጠወ ወወሀበ ቤዛ ኩሉ እንዲል፡፡
‹‹ ከመ ይሕየው ኩሉ ዘየ አምን ቦቱ እስከ ለዓለም ››
ይሕየው እስከ ለዓለም ኩሉ እሰከ ለዓለም ዘየአምን እስከ ለዓለም ብሎ ይገጥሟል፡፡ ኩሉ እስከ ለዓለም እስከ ምጽአት ድረስ የሚነሣ ትውልድ ሁሉ፡፡ ዘየአምን እስከ ለዓለም እስከ ምጽአት ድረስ የሚያምንበት አለ ከዚያ በኋላ ያመኑት እምነት ኤጠቅምምና፡፡ ከዚያ በኋላስ አይሁድስ እንኳ እፎኑ ርእር ታመጽእ አሚነ እንዲል እ ኮነ ወልደ ዕጓለ እመሕያው ወለቅዲሳን ኮነት ርስቱ ይላሉ አይጠቀሙበትም እንጂ፡፡ ይሕየው እስከ ለዓም ፍጻሜ የሌለው እስከ ነው ኢተመይጠ ቋዕ እስከ አመ ነትገ ማየ አይኀ፡፡ ኢወለደት ሜልኮል እሰከ አመ ሞተት እንዲል፡፡
‹‹ፈነወ ለነ መዝራዕቶ ልዑለ›› ልዑል ክንዱን ረቂቅ ክንዱን ሰደደልን ፈነወም ቢል በሥጋ ነው እንጂ በመለኮቱ አይደለም እፎኑ የፌንዎ በመለኮቱ ዘእንበለ ዳዕሙ በትስብእቱ ዘነሥኦ በአምሳሌ ላዕከ ይፌንዎ በአምሳለ ላእከ እንዲል፡፡ ክንድ አለው የሰው ኀይሉ በክንዱ እንዲታወቅ የአብም ኀይሉ በወልድ ታውቋልና፡፡ አንድም ክንድ ከአካል ሳይለይ የወደቀውን ዕቃ አንሥቶ ይመለሳል እርሱመ ከአብ አንድነት ሳየለይ አዳምን አድኗል፡፡ አንድም በከንድ የራቀውን ያቀርቡባል የቀረበውን ያርቁበታል በርሱም ጸድቃንን ንሁ ኃቤየ ብሎ ያቅርብበታል ኃጥአንን ሑሩ እምኔየ ብሎ ያረቅበታልና፡፡
‹‹ ሰአሊ ለነ ቅድስት፡፡››
እዱ መዝራዕቱ ከሚባለው ልጅሽ ፅንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኝልን፡፡
ዘሀ ሎ፡፡
እምቅመ ዓለም የነበው፡፡
ወይዘሉ፡፡
ዓምን አሳልፎ የሚኖረው፡፡
አመጸአ፡፡
ለኪነት ሥጋ የመጣው፡፡
‹‹ ወካዕበ የመጽእ ኢየሱስ ክርስቶስ ቃል ዘተሰብአ እምኔኪ ዘእነበለ ውላጤ፡፡››
ዳግመኛ ዓለሙን ለማሳለፍ የሚመጣው፡፡ ካንች ሳይለወጥ ሰው የሆነው አምላካዊ ቃል ኢየሱስ ክርሰቶስ፡፡
‹‹ ኮነ ፍጹመ ሰብአ፡፡››
ፍጽም ሰው ሆነ፡፡ ሰው የሆነውን ሰው ሆነ ማለት መንድር ነው ቢሉ ፍጹመ ለማለት ደገመው፡፡ አንድም ዘሀሎ፡፡ እምቅድመ ዓለም የነበረው ወይሄሉ፡፡ ዓለሙን አሳልፎ የሚኖረው ነው፡፡ ዘመጽአ፡፡ ዓለሙን አሳልፎ የሚኖረው ለኪነተ ሥጋ የመጣው ነው፡፡
‹‹ ወከዕበ የመጽእ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ቃል ዘተሰብአ ዘእንበለ ውላጤ፡፡››
ለኩነተ ሥጋ የመጣው፡፡ ዳግመኛ ዓለሙን ለማሳለፍ የሚመጣው ነው፡፡ ደግመኛ ዓለሙን ለማሳለፍ የሚመጣው፡፡ ካንች ሳይለወጥ ሰው የሆነው አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ኮነ ፍጹመ ሰብአ፡፡ ፍጸም ሆነ፡፡ ትቅስ ወኢተዋሐደ በመንፈቀ ህላዌ በኢኮነ ካልአ እንስሳ ዘበአንትጎ፡፡ አላምሉዕ ወፍጹም ውእቱ በአሐዱ ሀላዌ የገብር ዘክልኤቱ ህላዌያት እንዲል፡፡ ከዚህ ነፍስ አልነሣም፡፡
ምትሐት ኀድት፡፡ ተለወጠ የሙሉ መናፍቃን አሉና ለዚህ ያመታል፡፡
‹‹ ኢተበዓደ ወኢተፈልጠ በኪሉ ግብሩ ወልድ ዋሕድ፡፡››
አሁን ነፍስ አልነሣም ምትሐት ላሉት ይመልሳል፡፡ ተቀዳሙ ተካታይ የሌለው ወልድ ዋሕድ በሥራው ሁሉ ከኛ አልተለየም፡፡
‹‹አላ አሐዱ ራእይ፡፡››
አንድ ግብር ነው እንጂ፡፡
‹‹ወአሐዱ ህላዌ፡፡››
አንድ ባሕርይ ነው እንጂ፡፡ ወአሐዱ፡፡
አንድም ነው እንጂ፡፡
ሠስት ጊዜ አሐዱ አሐዱ አሐዱ አለ በሦስት ወገን የመስለናል በኀይለ ዘርዕ በኀይለ ንባብ በኀይለ እንስሳ፡፡
‹‹ መለኮት ዘእግዚአብሔር ቃል፡፡››
አካላዊ ቃል አንድም አሁን ጎድረት ላለው ይመልሳል፡፡ ተቀዳሜ ተከታይ የሌለው ወልድ ዋሕድ በሥራው ሁሉ ከነሣው ሥጋ አልተለየም፡፡
‹‹ አላ አሐዱ ራእይ፡፡››
አንድ ግብር ነው አንጂ፡፡
ወ1ዱ ህላዌ አንድ ባሕርይነው እንጂ፡፡
‹‹ ወአሐዱ መለኮት፡፡››
አንድ አካል ነው እንጂ፡፡
እስመ 3ቱ ኁልቁ መለኮቱ እንዲል፡፡ እንድም ተለወጠ ላሉት ይመልሳል፡፡ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው ወልድ ዋሕድ ሰውም ቢሆን ከአብ ከባሕርይ አባቱ ከመንፈስ ቅዱስ ከባሕርይ ሕይወቱ አለተለየም፡፡
እላ አሐዱ ራእይ፡፡
አንድ ኀብረ መልክእ ነው እንጂ፡፡ ወአሐዱ ህላዌ፡፡ አንድ ባሕርይ ነው አንጂ፡፡ ወአሐዱ መለኮት፡፡ አንድ አገዛዝ ነው አንጂ፡፡ ውስተ ኩሉ በሐውረት መለኮቱ እንዲል፡፡
‹‹ ዘእግዚአብሔር ቃል፡››
አካላዊ ቃል፡፡
‹‹ ሰአሊ ለነ ቅድስት፡፡››
ይቆየን የዕለተ ሰኞ ክፍል 2 በሚከጥለው ሳምንት ይቀጥላል:: ............ቸር ያቆየን!!!!!

No comments:

Post a Comment