Monday, August 9, 2010

ቅዳሴ ማርያም አንድምታ ክፍል 3

ኦ አበዊነ ንቡራዊነ እድ ስዩማን አለ መትልወ ሐዋርያት፡፡
አንቀጽ ተስማሚውን ያወርዳል፡፡ ናፈቅረክሙ ወነአብየክሙ ሲል ነው፡፡ ተውህበ ጳውሎስ ሙቁህ ብሎ ወአካል አንሂ መቁሃን ባለ ጊዜ ተወህቡ፡፡ አገብአ ለኤልዛቤል ወስተ ምስካባ ዘቀዳሚ ወእለሂ ዘመው ምሳሌሀ ባለ ጊዜ አገብጾሙ፡፡ ትህምክህሙ ቤተ ክርስቲያን አንተ ውስተ ባቢሎን ዘግብጽ ብሎ ወማርቆስ ባለ ጊዜ ይኤምኃ ክሙ እንዳለበት፡፡ ከሃዋርያት ቀጥላችሁ ሃዋርያትን መስላችሁ በአንብሮተ እድ የምትሾሙ አባቶቻችን እናከብራቸዋለን እናገኛቸዋለን፡፡ ከሊቀ ጳጳስ ጀምሮ እስከ ቄስ ያሉት በአንብሮተ እድ ይሾማሉ፡፡ ቅብዓት ያለበት ነው ዲያቆን በአንብሮተ እድ ይሾማል ቅብአት የለውም ከዚያ በታች ያሉትን በቃል ይሾሟቸዋል፡፡
እስመ ነሳእናከሙ አስተብቋዕያነ ለነ ለኀበ እግዚአብሔር፡፡

ወደ እግዚአብሔር ልታማልዱን፡፡ አስተበቁዐነ፤ እግዚአብሔር አግኝተን ተቀብለናችኋልና እናከብራችኋለን እናገናችኋለን ሃተታ፡- ሊቀ ጳጳሱ በሞተ ጊዜ የበቁትን ደጋጎቹን መርጠው ስማቸውን በቅፋፍ ጽፈው ያለፈው ኦ እግዞኦ አዕርፍ ነፍሰ አቡነ እገሌ ለሚመጣው ኦ እግዚኦ አንብር ለነ ዲበ መንበሩ ኖላዌ ሄረ ኢንኩን ከመ መር ኤት ዘአልቦ ኖላዊ ወኢይምስጠነ ተኩላ መሳጢ እያሉ ይፀልዩበታል፡፡ ፀሎታቸውን ሲፈጽሙ አንድ ብላቴ አምጥተው እያነሳህ ስጠን ይሉታል እያነሳ ይሰጣቸዋል ሳያይ መልሰው ይቀላቅሉታል አንዱን 3 ጊዜ መላልሶ ይሰጣቸው እንደሆነ ያሮስ ያሮስ አኪዮስ አኪዮስ ብለው ይሾሙታል ይደልዎ ይደልዎ ማለት ነው አንዱን 1 ጊዜ አንዱን 1 ጊዜ የሰጣቸው እንደሆነ ግን ከጸሎቱ ይጨምሩበታል ከሐዋርያት ሲያያዝ የመጣ እንደሆነ ይሁዳ በወጣ ጊዜ በይሁዳ እግር እኛ ባወቅን ማትያስ እና ባርናባስን መርጠናል አንተ እገግዚኦ ማእምረ ኩሉ ልብ አርኢ 1ደ እምአሉ ዘኃረይከ ዘይነስአ ለመልእክተ ሲመት ዘሐዋርያት፡፡ ኩላሊት ያመላለሰውን ልቡና ያሰበውን መርምረህ የምታውቅ አቤቱ ይህችን ሐዋርያተን ሹመት ገንዘብ የሚያደርጋትን ከነዚህ ከሁለቱ የመረጥከው አንዱን ግለጥልን ብለው፡፡ በአስተ አጸውዎሙ ይላል፡፡ እጻ አጣጣላቸው ወወዕአ ላእለ ማትያስ ይላል እጣ በማትያስ ወጣ መከራ የሚቀበልበት ነውና በዓለ፡፡ አንድም ለማትያስ ዋጋ የሚያገኝበት ነውና ለ አለ ወተኁለቁ ምስለ 0 ወ 1 ሐዋርያት ከ01 ሐዋርያት 02ኛ ሁኖ ተቆጥሯልና እንዲህ አለ፡፡
ወነሳእሙ በመዋእሊነ አስተሳሰብ ቋዕያነ ለነ ለህበ እግዚአብሔር እሎንተ 2 ኤተ ሊቀነ ጳጳሳት፡፡


የእስክንድርያ ሊቃነ ጳጳሳ እለ እስክድርስና አትናቴዎስን ወደ እግዚአብሔር ሊያማልዱን ተቀብለናአዋልና አስተበቁዐነ ይላል፡፡ እግዚአብሔር አግኝተን ተቀብለናቸዋልና እናገኛቸዋለን እናከብራቸዋለን ሃተታ፡- ዕለ እስክንድሮስ አርዮስን ተከራክሮ ረትቷልና አትናትዮስም በእሱ ሃዘን በርሱ ፀሎት በዘመኑ አርዮስ ሙቶዋልና፡፡
ብጹእ ጳጳስ አባ እገሌ ዘሀገር እስክንድርያ አባይ እስክንድርያ፡፡ በእስክንድርያ በመዲናይቱ ሀገር የተሸመ አባ እገሌን፡፡
ወዲበ ርእሰ ሃገረ አበዊነ ብጹእ ከጳጳስ በመዲናይቱ በአክሱም የተሸመ ንዑድ ክቡር የሚሆን አባ ሰላማን እንወደዋለን እናከብረዋለን እንዳለፈው ተርክ፡፡
አንድም አሎንተ ክልኤተ ሊቃነ ጳጳሳተ አባ እገበሌ ዘሀገር አባይ እለ እስክንድርያ ወዲበ ርእሰ ሀገረ አበዊነ ብፁእ ጳጳስ አባ ባስሊዎእ፡፡
የእስክንድርያውያን አባ እገሌ የሀገራችን ጳጳስ አባ ባስልዮስን እናከብራቸዋለን እነወዳቸዋለን እንክንድራውያንስ ሊቀጳጳስ ይሁን የሀገራችን እለምን ሊቀጳጳስ አለው ቢሉ እስክንድሪያው ሊቀ ጳጳስ አስጠግተ ስምኦንን ከሌዊ አስጠግቶ ካህናትን ህሉፋነ ፍኖት ከበቱ ፍኖተ እግዚኦሙ እንዳለ አንድም ከሊቀ ጳጳስ ማዕርግ አድርሶ የሚሰደው እለሆነ በመንበሩ አስቀምጦ ጭራውን መቋሚያውን መስቀሉን ሰጥቶ የሚሰደው ሰለሆነ አንድም ስም ሰጥተው ግብር ነስተውታል ወያክብርዎ በስመ ሊቀናት በህቲቱ ዘንበለ ይኩን ሎሩ ስልጣነ ዝንቱ እንዲል በእእክንድር እስክንድርያ ተብላለች፡፡ ታሪክ እስክንድር የሚባል ገናና ንጉስ ነበረ ስነ ባዓል ለማየት መንግስት ለማድረስም ቢሊ ለሌላም ነበር ቢሉ አንድም ያቁመን ለመተጋት እየሩሳሌም ወጣ ከወጣ ዘንድ ሲመለስ ሰም የሚያስጠራ ልጅ የለኝ ምን ሰርቼ ስሜን ላስጠራ አለ ድልድይ ሰርተህ አስጠራ አሉት ይህች እስክድርያ ማይ ጽንፋ ማይ ሃጹራ ይላታል ውሃውን በመዘውር በልሶ የብረት አምድ እያቆመ የብረት ድልድይ እየደለደለ በኖራ እየገለበጠ በብረት እየጠረቀ የብረት ሰረገላ እያሸጋገረ የብረት መረባ ሰርቷል፡፡

ልማደ ሰብእ ልማደ እንስሳ የሚወርድበት እንደ መሽረብ ያለ ሰርቶ አዞ ጉማሬ እየወጣ እንዳያውክ ገባሬ ተአምር አመጽ ኤልሳእን ቀብሮበታል በዚያ ላይ ሶስት ድስት ሙሉ ቀብሮበት ሂዷል፤ ይህ የተደረገ በዘመነ ቡሉይ ነው ሲያያዝ ከዘመነ ሀዲስ ደርሷል ከዘመነ ሀዲስ እስከ ዘመነ ሊቃውንት ደረሰ አትናቴዎስ በእስክንድርያ ተሹሞ ሳለ በዘመኑ ረሀብ ሆነ፤ ወርቅ ተቀብሮ እያለ ነደያን እየተራቡ እመከመ ረከብኩ ሞገሰ መቅድመ አምላክየ እየሀድጎ ለዝንቱ አድራማሌቅ ሙክራበ ሰገል እያለ ሲጸልይ ተምኔቱ ሳይፈጸምለት ሞተ፡፡ ከሱ ቀጥሎ ቴዎፍሎስ ተሸመ እሱም በዘመኑ ረሀብ ሆነ ወለእመ ለከብኩ ሞገሰ በቅድመ አምላክየ እየሀድጎ ለዝንቱ አድራማሌቅ ምኩራበ ወገል እያለ ሲያዝን ይኖር ነበረ ኃላ ግን አልአርታ የምትባል የሮም ንግስት ብዙ ሰራዊት አስከትላ ሄደች ስለምን ቢሉ ለምናኔ ብዙ ሰው አስከትሎስ ምናኔ የለም ብዙ ገዳማተ ግብጽን እጅ ለመንሳት በገዳማተ ግብጽ ካቱ አበው ለመባረክ ከአበው አንዱ እሱ ነውና ወደ እሱ ሄደች አዝኖ አየችው ምነው አዝናሀል አለችው እኔ አላዝን ማን ይዘን ወርቅ ተቀብሮ እያለ ነደያን እየተራቡ አላት አታስኮሰትረውምን አለችው ባይቻለኝ ባንተ ጸሎት በእግዚአብሔር ረድኤት አስኮሰትርልሀለሁ ብላ ብታስኮሰትርለት ቴዳ ቴዳ የሚል ሶስት ድስት ሙሉ ወርቅ ተገኝቷል ቴዳ ማለት ታኦስ ማለት ነው ታኦስ የጌታ ስም የጌታ ለነደያን ይገባል ብሎ አንዱን ለነድያን መጽውቶሎታል አንዱን ቴዳ ማለት ቴዎዶስዮስ ማለት ነው ብሎ ለንጉሱ ሰዶለታል፡፡ ንጉሱም ለበረከት ያህል ከፍሎ አስቀርቶ መልሶ ሰዶለታል፡፡ በዚህ አብያተ ክርስቲያናትም ይነጽት ለነዳያንም ይመጸውተው አልታወቀም፡፡ አንዱን ቴዳ ማለት ቴዎፍሎስ ማለት ነው ይሄ የእኔ ገንዘብ ነው ብሎ በዚህ ሰባት ያህል አብያተ ክርስቲያናት አንጾበታል፡፡ ታቦተ እየሱስ ታቦተ ማርያም ታቦተ ሚካኤል ታቦተ ሩፋኤል በዘባነ አንበሪ የታነጸ በዚያ ጊዜ ነው ታቦተ ኤልሳእ ታቦተ ዮሐንስ መጥምቅ ይህ አንድ ወገን ነው፡፡

ታቦተ ኤልሳቤጥ ታቦተ መርቆሬዎስ ነው ወረቅ ስለተገኘባተ አባይ አላት ይሕስ አባ ሕርያቆስ የሚሻ መንፈሳዊ የስጋው የደሙን ነገር ነው የመንፈሳዊ የስጋው ደሙን ነገር ሲናገር መጥቶ ማሩን አምርሮ ወተቱን አጥቁሮ ወርቅ ተገኘባት ብሎ አባይ አይላትም ብሎ ወትከውን አሃቲ ሀገር ምስዋኦ ለእግዚአብሔር እንዲል በአራቱ ማዕዘን ሐይማኖት ሲጠፋ እሰከ ዕለተ ምፅሐት ወልድ ዋህድ ስትል ትኖራለችና ርእሰ አክሱም ሀገር መላ ኢትዮጵያ፡፡
01 ይ ዲ በእንተ ብፅእት፡፡
ወብጽእት አንቲ እንተ ተአምኒ ከመ ይከውን ቃል ዘነገሩኪ ተብላ በኤላሳቤት ቃል ስለተመሰገነች፡፡
ወፍስሕት፡፡
ተፈስሂ ተፈስሂ ተብላ በመልአኩ በገብርኤል ቃል ስለተበሰገነች ወስብሀት ለኩሉ፡፡
ክብር በውስተ ነብያ ክቡር በውስተ ሊቃውንት እንዲል በሁሉ ዘንድ ስለተመሰገነች ወቡሩክት፡፡
ቡሩክት እንቲ እምአንስት ተብላ ስለተመሰገነች፡፡
ወቅድስት ወንጽህት እግዝእትነ ወላዲተ አምላክ ማርያም ድንግል ንጽህት ኩሉ ጊዜ ተብላ ስለ ተመሰገነች አምላክን ስለወለደች ስለ እመቤታችን ብለህ አንድም እሷን አማለጅ በማድረግ እጣን ቋጥረው ግብር ሰፍረው መባዕ ይዘው ወደ ቤተ እግዚአብሔር የሚሄዱት አስባቸው ይበል፤ እግዝእትነ እለ ከግብርናተ ዲያቢሎስ ነጻ አውጥቶ የሚገዛን ከእሷ በነሳው ስጋ ስለሆነ ነው፡፡
02 ወበእንተ ቅዱሳን ክቡራን፡፡ ጽኑዓን ክቡራን፡፡
መንፈሳውያን፡፡ ረቂቃን ስለሚሆኑ፡፡ ሊቃነ መላእክት፡፡
መዐርጋቸውን መናገር ነው፡፡ ሰማያውያን፡፡
ቦታቸውን መናገር ነው፡፡
ወኃያላን፡፡
ኃያላን ስለሚሆኑ ስለዚህ ብለህ አንድም በእነዚህ አማላጅነት፡፡ ሀተታ፡- በተፈጥሮ ኃይል ይሰጣቸዋልና አንድም በቅዳሴ በተራድኦ ምክንያት ይጨመርላቸዋልና፡፡
ሰባኪ፡፡
ነስሁ እስመ ቀረበት ምነግስተ ሰማያት እያለ፡፡
ወጸያሄ ፍኖት ዮሐንስ መጥምቅ፡፡ ጺሁአ ጸፍቶ እግዚአብሔር እያለ ስለሚያስተምር መጥምቀ መለኮት ስለሚሆን ስለዮሐንስ ብለህ አንድም በእሱ አማላጅነት፡፡
ወበእንተ ቅድሳን ስቡሃን ወላእካን ማትዮስ ወማርቆስ ሉቃስ ወዮሐንስ 4ቱ ወንጌላውያን፡፡
ንጹሀን ክቡራን ላእካነ ቃል ስለሚሆኑ ስለ 4ቱ ወንጌላውያን ስለ ማቴዎስ ስለ ማርቆስ ስለ ሉቃስ ስለ ዮሐንስ ብለህ አንድም በዚህ አማላጅነት ማቴዎስና ዮሐንስ ከቦታቸው ይተረጎማሉ፡፡
ማርቆስ ማለት አንበሳ ማለት ነው አንበሳ ለላህም ጌታው ነው ይሰብረዋል፡፡ እሱም ከግብጽ ላምህን አጥፍቷልና አንድም ንህብ ማለት ነው ንብ የማይቀስመው አበባ የለም፤ እሱም አስቀድሞ ከጌታ ኋላ ከኃዋርያት ተምሯልና አንድም ካህን ማለት ነው ወአምጽኡ ማረዜድዮስ እንዲል፡፡
ሉቃስ ማለት መስበር ማለት ነው ብስራት ማለት ነው ብስራት መልአክን ይጽፋልና አንድም ተንሳኢ ማልት ነው ለስብከተ ውንጌል ይጠናልና አንድም አቃቤ ስራይ ማለት ነው፡፡ ዘስጋ ነበረ ኃላ ግን አቃቤ ስራይ ዘነፍ ሁኗልና፡፡
03 በእንተ ቅዱሳን አግብርቲከ ክቡራን ባለሟሎችህ ስለሚሆኑ ሀተታ፡- የባለሟልነት ስማቸው ነው ዳዊት ገብርየ ሙሴ ገብርየ እንዲል፡፡
ጴጥሮስ
ጴጥሮስ ማለት መሰረት መሰረትነቱ የሀይማኖት የልጅነት ነው፡፡ ወያእቆብ ስለያዕቆብ ብለህ ያዕቆብ ማለት አእቃጼ ሰኮና አሃዜ ሰኮና ማለት ነው የቀደመው የዕቆብ ሰኮና ኤሳውን ይዞ እንደተወለደ እሱም ወንጌል ሲያስተምር በዚያው ይሞታልና አእቃጼ ሰኮና ኤሳው እንደሆነ በትምህርቱ የመናፍቃንን ትምህርት ያሰናክላልና፡፡
ወዮሐንስ
ስለ ዮሐንስ ብለህ ዮሐንስ ፍስሐ ወሐሴት ርህራሄ ወሳህል ማለት ነው ፍስሃ ወሀሴት አለ ቅብአ ትፍስህት መንፈስ ቅዱስ ያስጣልና ርህራሄ ወሳህል አለ በጸጋ ዘነሳእክሙ መጸጋ ሀቡህ በእንቱ ዘነሳእክሙ በከንቱ ሀቡ ባለው ጸንቶ ያስተምራልና፡፡
ወእንድርያስ
ስለ አንድርያስ ብለህ አንድርያስ ማለት ተባእለ ለመስቀል በኩረ ሐዋርያተ ማለት ነው ተባእ ለመስቀል አለ እስከ ሀገር በላእተ ሰብእ ሄዶ አስተምሯልና፡፡
ፊሊጶስ
ፊሊጶስ ማለት ምፍቀሬ አኅው ማለት ነው ፊልሳዳፎስ እንዲል አንድም አሃዜ ኪናት ረያጺ አፍራስ ማለት ነው አንድም ስውር ቦታ ማለት ነው ፌላሌምሎሞንም ንዑ ንህድር ብሔር ፊልሞን እንዲል፡፡
በርተለምዮስ
ስለ በርተለምዮስ ብለህ በርተለምዮስ ማለት ተክል የማጠጣት ግብር ያለው ልጅ ማለት ነው፡፡ ኩን ወልደ ኃይል ኩን ወልደ የማን እንዲል፡፡ አንድም ዕለቱን ወይን ተክሎ ለመስዋእት አድርሷልና፡፡
ቶማስ
ስለ ቶማስ ብለህ ቶማስ በለት ፀሀይ ማለት ነው ሁለቱ አስማቲሁ ለፀሀይ 1ዱ ኦርያሬስ ወካልኡ ቶማስስ እንዲል፡፡ ወማቴዎስ
ስለ ማቴዎስ ብለህ ማቶዎስ ማለት ህሩይ እመጸብሀን ማለት ነው ግብር የሚያስገብርበት መርጦታልና፡፡
ወያዕቆብ ወልደ እልፍዮስ
ስለ ያዕቆብ ወልደ እልፍዮስ ብለህ ወልደ እልፍዮስ ማለት ተለይቷል አንጂ ትርጓሜው እንዳለፈው ነው፡፡
ታድዮስ
ስለ ታድዮስ ብለህ ታድዮስ ማለት ዘርእ ወማእረር ማለት ነው ኦርቲን እንደዘር ወንጌልን እንደማእረር አድርጎ አስተምሯልና አንድም ዕለቱን ሰንዴ ዘርቶ ዕለቱን ለመስቀእት አድርሷልና፡፡
ወስምኦን ወማትያን
ሰለ ስምኦንና ሰለማትያን ብለህ ማትያን ማለት ምትክ ማለት ነው ማትያስ ማለት ፀሐይ ማለት ነው፡፡
0ቱ ወ2ቱ ሐዋርያት፡፡
ስለ አስራ ሁለቱ ሐዋርያት ብለህ አንድም በእነዚህ አማላጅነት አስባቸው ስማቸውን አስቀድሞ ቁጥራችን ወደኋላ አመጣ
ወያዕቆብ ሐዋርያ እኁሁ ለእግዚእነ ኤጰስ ቆጰስ ዘኢየሩሳሌም፡፡ በኢየሩሳሌም ኤጲስ ቆጶስነት ስለተሸመ የጌታችን ወንደም ስለሚሆን ስለ ወንጌል ዙሮ ስለእስተማሩ ስለያእቆብ ወንጌልን ዙሮ ስለ አስተማሩ ያዕቆብ ብለህ አንድም በእሱ አማለጅነት ሀተታ መገናኛው ጉንዱ አልኣር ነውአልአዛር ቅስራንና ማትያንን ይወልዳል ቅስራ እያቄም እመቤታቸንን ጌታን ማትያን ያዕቆብ ዮሴፍን ዮሴፍ ያዕቆብን ይወልዳል፡፡ በአንፃር ያለ ነውና እኁሁ አለ፡፡
ለተዘምዶ እነ ያዕቆብ እነ ዮሐንስ ወለደ ዘብድዮስ ይቀርቡታል ብሎ እናቱ በህጻንነቱ ሙታ ከአባቱ ቤት አግኝታው ከጌታ ጋር እያጠባች አሳድጋዋለችና ኃሊብ ድንግልናዊንስ እሩቅ ብእሲ መጥባት አይቻለውም ብሎ እንደ እናት ሁና ኣድጋዋለችና ኤጲስ ቆጰስ ዘእየረሳሌም አለ ያዕቆብ መኮነ እግሩ ከመ እግረ ነጌ ይላል ከገድል ጽናት የተነሳ እግሩ እንደሙቀጫ ተድበልብሎ ነበር እና ለስበከተ ወንጌል አይፋጠንም ብለው በኢየሩሳሌም ሹመውት ሄደዋል፡፡ ከሀዋርያት አንድ አንድ ደዌ የሌለበት አለ ቅዱስ ጴጥሮስንም ወኮነ ድውየ ወድግዱገ ስጋ ይለዋል አጸናበትም አንጂ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ቀጭን ሰጥር ውጋት አዳጊት የምትባል ራስ ፍልጠት ደዌ ነበረበት በእዚያውስ ላይ ሐዋርያ ደመና ጠቅሶ ካሰበው ደርሶ ብዙ አስተምሮ አሳምኖ ብዙ አጥምቆ ይውል የለምን ቢሉ በኢየረሳሌም የነበሩ አይሁድ ምሁራነ ምፃሕፍተ ነቢያት ናቸው ከእርሱ በቀር የሚያውቅባቸው የለም ብለው ሹመውታል ያገሩን ሰርዶ ባገረ በሬ እንዲሉ፡፡ ሐዋርያ አለው ወንጌል ዙሮ አስተምሯልና
ወቅዱስ ወስቡህ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት ወቀዳሜ ሰማእት፡፡
ንጹህ ክቡር ሊቀ ዲያቆናት የሰማዕታት ደገኛ አንድም የሰማእታት ፊታውራሪያቸው ስለሚሆን ስለ እስጢፋኖስ ብለህ አንድም በእሱ አማላጅነት እስጢፋኖስ ማለት ወደብ መደብ ለሆቴ ደንጊያ ማኅቶተ ቁድ ማለት ነው ንፋስ የማያስገባ ብርሃን የማይከለክል ፋና ነው ቀዳሜ ሰማዕት አለ ከጌታ ቀጥሎ ከሐዋርያት አስቀድሞ መከራተ የተቀበለ እሱ ነውና 6ቱን ዲያቆናት መርጠው 7ኛ እርሱን መደበኛ አድርገው ሹመውታልና ሊቀ ዲያቆናት አለ፡፡
04 ወኩሎሙ ቅዱሳን ወሰማእት እለ እረፉ በርትእት ሐይማኖት፡፡
ውሎ ውሎ ከቤት ኑሮ ኑሮ ከመሬ እንዲሉ ኃይማኖታችንን አንክድም ብለው ስለሞቱ ሰማእታት ብለህ አንድም በነዚህ አማላጅነት፡፡
ጳውሎስ
ስለ ጳውሎስ ብለህ አንድም በእሱ አማላጅነት ጳውሎስ ማለት ነዋየ ህሩይ ማለት ነው፡፡
ጤሞቲዎስ
ስለ ጤሞትዮስ ብለህ ጤሞትዎስ ማለት ዘአልቦቱ ጥሬት ማለት ነው፡፡
ሲላስ
ስለ ሲላስ ብለህ ሲላስ መለት ፀሐይ መለት ነው፡፡
ወበርናባስ
ስለ በርናባስ ብለህ በርናባስ ማለት ወልደ ፍስሀ ማለት ነው፡፡
ቲቶ
ስለ ቲቶ ብለህ ቲቶ መለት አርቅ ማለት ነው፡፡
ወፍልሞና
ስለ ፍልሞና ብለህ ፍልሞና ማለት ስውር ቦታ ማለት ነው፡፡
ወቀሌምንጦስ
ስለ ቀሌምንጦስ ብለህ ቀሌምንጦስ ማለት ግንብ ማለት ነው፡፡
፸ወ2ቱ አርድዕት
ነሣሣለትና ስለ ሰባሁለቱ አርድዕት ብለህ አንድም በእነዚህ አማላጅነት አስባቸው፡፡
5ቱ ፻ት ቢጽ፡፡
ስለ አምስት መቶ ቢጽ ብለህ አንድም አንዚህ አመላጅነት በማድረግ ሀተታ፡- እሊህ ከ5፻ ብቅ 6፻ ዝቅ እንደሚሉ በዕለ አርብ እንደ አሸን ፈልተው ከእግረ መስቀል የተነሱ ናቸው ቢጽ አላቸው በተፈጥሮ ከእሊህ እስከ እርገት እስከ ጰራቅሊጦስ ያስተማረ አለ ወዲያው እስከ ትንሳኤ ቆይቶ ያረፈ አለ፡፡
3፻0ወ8 ርቱዓነ ሀይማኖት፡፡
ሃማኖታቸው ስለ ቀና ስለ ሶስት መቶ አስራ ስምንቱ ሊቀውንት ብለህ አንድም እነዚህን አማለጅ በማድረግ እጣን ቋጥረው ግብር ሰፍረው መብዓ ይዘው ቤተ ክርስቲያን የሚሄዱትን አስባቸው አንድም እንዚህ አማላጅ ስለአደረጉ፡፡ አንድም በእነዚህ አማላጅነት አስባቸው፡፡
05 ለእሉኒ ወለኩሎሙ ተዘከሮሙ ለከ እግዚኦ፡፡ ያለፈውን የሚያጣራውን ላንተ ማደሪያ ቤተሰብ ወገን ለሚሆኑ አቤቱ አስባቸው፡፡
ለብጹእ ወለቅዱስ ሊቃነ ጳጳስ አባ እገሌ ንዑድ ክቡር የሚሆን አባ እገሌን፡፡
ወብዑእ ወቅዱስ አባ እገሌን፡፡ ንዑድ ክቡር የሚሆን አባ እገሌን አስባቸው አንድም ለእነዚህ ብለው እጣን ቋጥረው ግብር ሰፍረው መብዐ ይዘው ወደ ቤተ እግዚአብሔር የሚሄዱትን አስባቸው፡፡
06 ከመ ትዕቀቦሙ በሕይወቶሙ በሕይወተ ስጋ ሳሉ ከመከራ ስጋ ትጠብቃቸው ዘንድ አንድም ማሰብ ሌላን ዓለም ጠብቃቸው፡፡
ወታድኅኖሙ፡፡
ታድናቸው ዘንድ፡፡ አንድም ማዳን ሌላን አለ አድናቸው፡፡
ወትሥረይሎሙ አጢአቶሙ፡፡
አጢአታቸው ታስተሰርይላቸው ዘንድ አንድም ማዳን ሌላን አለ ኃጢያታቸው የሚያስተርይላቸው
ወትምሀረነ ኪያነ ሂ በጸሎተ እግዚእሆሙ ለዓለን ዓለም፡፡
ትምሀረነ ካለ ለነሂ ኪያነ ካለ ትምሀር ባለ በቀና ነበረ ነገር ግን ልማደ መጽሀፍ ነው እኛንም በእሳቸው ጸሎት ይቅር ትለን ዘንድ አንድም ማሰብ መጠበቅ ማዳን ኃጢያትን ማስተሰረይ ሌላን አለ በሳቸው ጸሎት ለዘለዓለሙ ይቅር ይበለን፡፡
ይቆየን .........

No comments:

Post a Comment